በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የካህናት እና ምዕመናን ኅብረት

CORRESPONDENCE

EOTCCPA PR 080423-Final (2).pdf

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን ኅብረት የአቋም መግለጫ

August 8, 2023 10:48pm

ነ ሐ ሴ ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም

EOTCCPA- RE20151201

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕሕዶ ቤተ ክርስቲያን

ካህናትና ምዕመናን ኅብረት የአቋም መግለጫ

“በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜንአሜን!”

መለየት የሚወድድ ምኞቱን ይከተላል፥ መልካሙንም ጥበብ ሁሉ ምሳ 18፡1

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዘንድሮው ዓመት በተደጋጋሚ የተከሰተው ቀኖናንና ሥርዐተ ቤቤተ ክርስቲያንን በጣሰ መልኩ በዘረኝነት መንፈስ በመሸነፍ የተለያዩ አባቶች ለ የራሳቸው በሚያመች፣ ነገር ግን ሕገ ቤተ ክርስቲያንን በሚያፈርስ ፣ የቤ ተ ክርስቲያንን አንድነት በሚንድ መልኩ የተለያዩ ሹመቶች ን በ ማከናወን ለቤ ተ ክርስቲያንና ለቅዱስ ሲኖዶስ ከባድ ፈተና የታየበት ዓ መት ነው።

ቅዱስ ሲኖዶስም ስህተቶች በተፈጠሩ ቁጥር ለቤ ተ ክርስቲያን አንድነት ይበጃል የሚለውን እርምጃ ሲወስድ ቆይቶአል። እነዚህን ክስተቶች ንም አስመልክቶ የሰሜን አሜሪካ የካህናትና ምእመና ኅብረት ካምኅ ጉዳዮቹን በ ጥልቀት እያጠና ፣ መጻኢ አደጋዎችንም እየተመለከት ፣ ሊሆን ይገባዋል የሚለ ው ን የመፍትሄ ሃሳቦች በተደጋጋሚ የአቋም መግለጫ በማውጣት የተለያዩ ብ ፁ አን አባቶችንም በማነጋገርና ኅብረቱ ያለውን ስጋት ና መፍትሄ ሊሆን ይችላል የሚለውን ቁም ነገሮችን በማስረዳት ከቅዱስ ሲኖዶስ ጎን በመቆም ለመፍትሄው ሲጥር ቆይቶአል። አሁንም ቀድሞ በ ጥር 14/ 2015 ዓ.ም የተከሰተው ሕገ ወጥ ሹመት በትግራይ ሃገረ ስብከት መከሰቱ እጅግ ልባችንን የሰበረና ችግሩ ከቅድሞ ው ይልቅ የ ኋ ለኛው ይብሳል እንዲል እጅግ የከፋ ችግር መሆኑን ተረድተናል። ቅዱስ ሲኖዶስም ይህንን አሳዛኝ ጉዳይ አስመልክቶ ሐምሌ ፳፮ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም ባካሄደው ምልዐተ ጉባኤ የተለዩ ውሳኔዎችንና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በመጠቆም ውሳኔ አሳልፎአል። በተመሳሳይ ሁኔታ የሰሜን አሜሪካ የካህናትና ምእመና ኅብረትኅብረትም ካምኅ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔና መግለጫ በመደገፍ የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

የአቋም መግለጫ

1) ቀድሞ በወርኃ ጥር በኦሮምያ ክልል እንደተደረገው ዛሬም በትግራይ አህጉረ ስብከት የተደረገውን የዘጠኝ ቆሞሳትን በኤጲስ ቆጶስነት ሾመናል በማለት ኢኢ-ቀኖናዊ ፣ ሕገ ወጥ የሆነና ሥር ዓ ተ ቤ ተ ክርስቲያንን ባል ተ ከተለ መልኩ፣ ለቤ ተ ክርስቲያን አንድነት ፀ ር ፣ ለ አ ገር አ ንድነት መናድ መሠረት ይሚጥልና የማን አልብኝነት ተግባር መሆኑን ካምኅ ይረዳዋል። የክርስትና እምነት ክርስቶስን በመ ምሰል፣ ፍኖተ ሐዋርያትን በመከትል ፣ የምንሄድበት ፣ ለመንጋው የምንራራ ለ ት ፣ በመቻቻል ፣ ስሕተትንም ፣ በመተራረም ቅዱሳንን በመ ም ሰል የምንሄድበት እንጂ፣ እልህ በመጋባት ና ራስን በመ ኮፈስ የ ሚኖር ሕይወት እንዳልሆነ መላው የ ቤ ተ ክርስቲያን አገልጋይ ሁሉ የሚረዳው እውነታ ነው። በትግራይ ክልል ባሳለፍናቸው ሦስት አመታት የተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነት ስሜት የማይሰጥ ፣ በጥቂት የፖለቲካ ኃይሎች ነገሮችን በጥሞና ለመ ወያየትና ለመግባባት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ምክንያት የተ ከሰተ መሆኑ አ ገር ያወቀው ፀ ሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። በዚህ ጦርነትም የተለያዩ የ አ ገሪቱ ክልሎች የጦርነቱ ገፈት ቀማ ሾ ች ቢሆ ኑም የትግራይ፣ የአማራ እና የአፋር ክልሎች ግን ከምንም በላይ ግን ባር ቀደም ሰለባዎች መሆናቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። ቤተ ክርስቲያንም ባለባት መንፈሳዊ ግዴታ ጦርነቱ ከመጀመሩ አስቀድሞ ወንድማማቾች በጋራ መድረክ እንዲመክሩ ለማድረግ ጥረት ብታደርግም በትግራይ ክልል ባሉ መንፈስ ዊ መሪዎች በኩል ይሰጥ የነበርው ምላሽ እና አጀንዳው እንዳይቀርብ ይደረግ የነበርው ጉትጎታ የቤተ ክርስቲያንን  ጥረት መና አድርጎታል። በጦርነቱ ወቅት ቅዱስ ሲኖዶስ በጀት አልሰ ጠ ንም ፣ ረስቶናል በሚል ሰንካላ ምክንያት በጠራራ ፀሐይ ቅጥፈት ራስን መገንጠልና ከሕገ ቤ ተ ክርስቲያን ውጭ መሄድ እጅግ አሳፋሪ ሲሆን፣ የዚህ ድርጊት አስፈጻ ሚዎችንም የስብእናና የሃይማኖት መረዳት ደረጃን አሳንሶ የሚያሳይ አካሄድ ነው። ስልሆነም በትግራይ ሃገረ ስብከት በሕገ ወጥ መንገድ ዘጠኝ ኤጲስ ቆጶሳትን ሹመናል ባሉ ግለሰቦችና ሹ መትን ተቀብለናል በሚሉ አደናጋሪዎች ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ ሐምሌ ፳፮ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም በሙሉ ድምጽ የወሰነውን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ የምንደግፍ መሆናችንንና ለውሳኔው አፈጻጸምም አስፈላጊውን ሁሉ እንደምናደርግ ልንገልጽ እንወዳለን።

2) ካለፈው ተሞክሮና ተግዳሮትም አንፃር ሕ ገ ወ ጥ ሿሚዎችና ተሿሚዎች በግልፅ ስህተታቸውን አምነው ና ቤተ ክርስቲያንን ይቅርታ ጠይቀውና ቀኖና ተቀብለው እስኪመለሱ ድረስ ቅዱስ ሲኖዶሱ ውግዘቱን እንዲያፀና እየጠየቅን፣ የ ሦስ ተኛ ወገን ሽምግልና አልፎ ተርፎ ጣልቃገብነት ን በጥንቃቄ እንዲመረምርና ማንኛውም ዐ ይነት የፖለቲካ፣ወይንም የመንግሥት ጣልቃገብነትን ባለመቀበል ለተፈጠሩት ችግሮች ቀኖና ቤተ ክርስቲያንና ሥርዐተ ቤ ተ ክርስቲያን ብቻ መሠረት ያደረገ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን ያካተተ ዘለቄታዊ መፍትሄ ን እንዲስጥ አበክርን በ ልጅነት መንፈስ እንጠይቃለን

3) የትግራይ ክልል ፖለቲከኞች ከማዕከላዊ መንግ ሥ ት ባለ ስልጣ ናት ጋር ደም ተቃብተው ከሚሊዮን በላይ የሚ ሆኑ ኢትዮጵያውያንን አለአግባብ ተሰውተ ዋል። ይሁን እንጂ ሁለቱ ቡድኖች ፣ ማለትም የማዕከላዊው መንግሥትና የክልል መንግሥት በሰላም ለመሥራት ሲስማሙ በአንጻሩ መንፈሳዊ የተባሉ አባቶች ግን ከዚህ አይነቱ ተባብሮ የመሥራት መንፈስ አፈንግጠው ቤተ ክርስቲያንን ማድማት መቀጠላቸው እጅጉን አሳዛኝ ነው። ይባስ ብሎ መላውን የትግራይ ሕዝብ ሲያሳጡ የነበሩ ፖለቲከኞች ክልሉን ሊጎበኙ በሄዱ ወቅት እኒሁ የትግራይ መንፈሳዊ አባቶች ከባእታቸው ወጥተው እጅ እየነሱ ባለሥልጣናቱን ተቀብለው አስተናግደው ሸኝተዋል። በአንጻሩ ደግሞ፣ ፍቅርንና የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ፈልገው ወደ ክልሉ የመጡትን የቅዱስ ሲኖዶስ ተወካይ አባቶች ላይ የቤተ ክርስቲያንን ደጃፍ በመዝጋት የቅዱስ ሲኖዶስ ልዑካንን ሳያነጋግሩ ያለውጤት እንዲ መልሱ አድርገዋቸዋል። ይህ ድርጊት የሚያሳየው የድርጊቱ ፈጻሚዎችና አስፈጻሚዎች በምን ያህል የወረደ ማንነት ውስጥ እንዳሉ የሚያሳይ ድርጊት ነው። አሁንም የትግራይ ሕ ዝበ ክርስቲያን በእረኞች እጦት እንዳይጎዳ ፣ ከቀሪው የ አ ገሩ ክርስቲያን ወገ ኖ ች ተነጥሎ ባዕድ እንዳይሆን ና ቤተሰባዊ ቁርኝት ከቀሪው የ አ ገራችን ሕዝቦችጋ እንዳይበጠስ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ የበላይ አስተባባሪነት በጥንቃቄ ተገቢው ድጋፍና አፅኚ ትምህርት እንዲሰጠው ፣ በቀጣይ ም መንፈሳዊ ትስስርም ክርስቲያናዊ ቤተሰብነቱ ተጠብቆ እንዲቆይ እንዲደረግ መን ፈሳዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን::

4) ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃ ይማኖት በአንድ ወቅት ሃይማኖታችን የደም ስራችን ነች በማለት ለቤ ተክርስቲያን አንድነት ያሳዩት አክብሮትና ፍቅር ሁሌም ከውስጣችን የማይወጣ ሃቅ ነው። ነገር ግን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም በትግራይ አህጉረ ስብከት በተከሰተው ስሁት ሹመት ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በሚያሳልፍበት ወቅት ከምልአተ ጉባኤው ጋር አብረው በጋራ አለመቆማቸው የቅዱስነታቸውን ለ ሃይማኖት ያላቸውን ቁርጠኝነት ጥያቄ ውስጥ አስገብቶታል። በዚህ ወ ሳኝ ወቅት መላው ጉባኤ በአንድ ድምጽ ሲቆምና ድርጊቱ ን ሲያውግዝ በቅዱስነ ትዎ በኩል ግን ከምልአተ ጉባኤው ጋር በጋራ አለመቆምዎ ብዙዎቻችንን ቅር ያሰኘ ኩነት ሆኖ አግኝተነዋል። ይህም አካሄድዎ ችግሩን ከማባባስ በቀር ለመፍትሄ ጋባዥ አለመሆኑ ግልፅ ነው። ስለሆነም ቅዱስነትዎ ነገሮችን በማስተ ዋ ል ከምንም ነገር በላይ ሃይማኖትና የህዝብን አንድነት በማስቀደም አቋምዎን ከቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤው ጋር እንዲያደርጉና ፣ እግዚአብሔር ለመላው የኢትዮጵያውያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች እረኛ አድርጎ እንደሾምዎ በማሰብ ቤተ ክርስቲያንን ከብ ፁአ ን አባቶች ጋር በአንድነት እንዲመሯትና ሊመጣ ያለውንም የከፋ መገነጣ ጠ ል እንዲያስቆሙ በታላቅ ትህትና በልጅነትም መንፈስ እንጠይቃለን።

5) በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮችና አገልጋዮች በሕገወጥ መልኩ የኤጲስ ቆጶስነት ማዕረግ አግኝተናል በማለት በአገር ውስጥም ከአገር ውጭ ይህ ሕገ ወጥ ቡድን እንቅስቃሴ እያደረገና ተሿሚዎችንም በየስፍራው እየላከ ይገኛል። ስለሆነም መላው ክርስቲያን እነዚህ ሕገ ወጥ ግለሰቦች በቅዱስ ሲኖዶስ ፍጹም የተወገዙ መሆናቸውን በመረዳት ፣ አገልጋዮችም ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን ስለጉዳዩ ግን ዛቤን በማስጨበጥ ከእነዚህ ከፋፋዮችና ቤተ ክርስቲያንን ከሚንዱ ፣ የአገርን አንድነት ከሚያፈርሱ ፣ ግለሰቦች እንዲጠበቁ እንድታደርጉ እያልን መላው ሕዝበ ክርስቲያንም የ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳ ኔን በማክበር ለአፈጻጸሙም የበ ኩላችንን አስትዋጽኦ እንድ ናደርግ የሰሜን አሜሪካ የካህናትና የምእመናን ኅብረት ካምኅ መልእክቱን ያስተላልፋለን።

6) ቤተ ክርስቲያን ያለባት ፈተና ፈርጀ ብዙ ሲሆን አንደኛው ለቤ ተ ክርስቲያን በመቆርቆር የሚደረጉ በየማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን የሚሰጡት ሃሳቦች ናቸው። ምንም እንኳን አብዛኛውን ጊዜ በእነዚሁ የመገናኛ ብዙሃን ላይ ብዙ ገንቢ ሃሳቦች የሚያንሸራሽሩ ቢሆንም በአንጻሩ ደግሞ የአባቶችንና የቅዱስ ሲኖዶስን ክብር ዝቅ በሚያደርግ ሁኔታ የሚገለጹ ነገሮች እንደሚከሰቱ የታዩ ጉዳዮች ናቸው ። ይህ አይነቱ አካሄ ድ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ብሎም ፍቅርን ከማጽናት ይልቅ መለያየትንና የቤ ተ ክርስቲያንን ገጽታ በሚያዛባ መልኩ በ ም እ መናን ዘንድ የተሳሳተ ና አወዛጋቢ ግንዛቤን ስለሚሰጥ አገልጋዮች ነገሮችን በጥሞናና በትእግስት ብሎም በብስለት እንዲመለከቱ ብሎም በማናቸውም የማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን የሚተላለፉ መልእክቶች የቤተ ክርስቲያንን ደረጃ የጠበቁ እንዲሆኑ መንፈሳዊ ጥሪ እያቀረብን ፣ መላው ክርስቲያንም በእነዚህ አይነቶች ደካማ ሃሳብ ምክንያት ለአባቶች ያለው ክብር እንዳይ ሸረሸርና ለ ቅዱስ ሲኖዶስም ተገቢውን አክብሮት እንዲሰጥ መልእክታችንን ልናስተላልፍ እንወዳለን።

በስተመጨረሻም ወቅቱ የሱባኤ ወቅት እንደመሆኑ መላው ሕዝበ ክርስቲያን ስለ አገራችን ኢትዮጵያ አንድነት ፣ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ጽናት በትጋት በመጾምና በመጸለይ ለእግዚአብሔር እንድናሳስብ ፣ እርስ በርስም በጸሎት እንድንተጋ መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን ።

                          እግዚአብሔር አምላክ አገራችንን ኢትዮጵያንና ቤተ ክርስቲያናችንን በ አንድነት ይጠብቅልን

                                                                                          ዋሺንግተን ዲሲ

                                                                                     ነሐሴ ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም

                                                                                      ( August 07, 2023)

በወቅታዊ የቤተክርስቲያን ጉዳይ pdf.pdf

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ የካህናትና የምእመናን ማኅበራት/ኅብረቶች በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የተሰጠ የጋራ መግለጫ 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ የካህናትና የምእመናን ማኅበራት/ኅብረቶች በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የተሰጠ የጋራ መግለጫ 

ሐዋርያዊት እና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በየዘመኑ የመጡባትን ፈተናዎች በእግዚአብሔር ቸርነት በቅዱሳን አባቶቻችን ጸሎት ፤ ቁርጠኛ አመራር እና ሰማዕትነት ፤ አንዲሁም በሕዝበ ክርስቲያኑ ጥብአት አልፋ ዛሬ የደረሰቸበት ደረጃ ትገኛለች። በፈተናዎች ውሰጥ ስታልፍ ሁሉን በአገባብ እና በሥርዓት አከናውና ፤ ሥርዓተ ቤተ ክርሰቲያን እና ቀኖናዋን አስጠብቃ ለዘመናት ኖራለች። ከነዚህም አንዱ ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ሲተላለፍ የመጣው የሥርዓተ ሲመት ቅብብሎሽ እና አፈጻጸም ነው።

 ኾኖም ግን ካለፉት ጥቂት አሠርት ዓመታት ወዲህ ይህ ቀኖናዊ ትውፊት እየተጣሰ፣ ሥርዓቱም እየፈረሰ መጥቷል። በተለይ መንፈሳዊው ሥልጣን በምድራዊና የጎሳ ፖለቲካ ስሌት እየተሰጠ ሲመጣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሊቃውንትና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላትን በተናጠልና በኅብረት ሲያወያይ ቆይቷል። እኒሁ ሊቃውንትም ለቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ ለኾነው ለቅዱስ ሲኖዶስ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ማሳሰቢያ ሲሰጡበት የቆየ ጉዳይ ነው። 

ይኽም ኾኖ መፍትሔ ባለመገኘቱ ምክንያት ከሦስትና አራት ዓመታት ጀምሮ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ምእመናን እና ወጣቶች በተለያየ መልክ በመደራጀት ሲመክሩ ቆይተዋል። በተጨማሪም እነዚሁ የተለያዩ ማኅበራትና ግብረ ኃይሎች የቤተ ክርስቲያኒቱን ወቅታዊ ችግር በመዘርዘርና የመፍትሔ ሐሳብ በመጠቆም ለቅዱስ ሲኖዶስ፣ ለቅዱስ ፓትርያርኩና ለሲኖዶሱ አባላት በተደጋጋሚ እስከ አሁኑ ሰዓት ድረስ በማሳሰብ ላይ ይገኛሉ። ይኹን እንጅ ችግሩ በመሻሻል ፋንታ እየተባባሰና እየከፋ ሂዶ ከላይ እንደተገለጸው ሐዋርያዊው የክህነት ቅብብሎሽ እና ሥርዓተ ሢመት ፈሩን ስቶ በጎሳ መር ፖለቲከኞች የተቃኘ እና ለሕገ ቤተ ክርስቲያን በማይገዙ አባቶች አስፈጻሚነት እየተከወነ ይገኛል። ለዚህም ዋቢ የሚኾነው በፈጸሙት ሕገ ወጥ ሢመትና ያንንም ተከትሎ ለብዙ ምእመናን ሕልፈተ ሕይወት ምክንያት በመኾናቸው ቅዱስ ሲኖዶሱ በጥር ፲፰ ቀን ፳፻፲፭ ዓ. ም. ያወገዛቸውን አባቶች መልሶ ከቀኖና ውጭ በየመንበራቸው ማስቀመጡና ይባስ ብሎም ከእኒሁ ተመላሽ አባቶች ለኤጲስ ቆጶሳት መራጭ ኮሚቴ ሰብሳቢ ማድረጉ ነው። ይህ አካሄድ ለማንኛውም ኦርቶዶክሳዊ በእጅጉ ልብ የሚሰብርና በቀጣይነትም የቤተከርሰቲያን አንድነትን የሚያናጋ ነው። ይኽ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደት በዚሁ ሁኔታ ከቀጠለ ቤተ ክርስቲያኒቱን በግልጽ ወደማትወጣበት አዘቀት ውስጥ የሚያስገባት መኾኑ እሙን ነው። በመኾኑም እነዚህ ከክርሰትና መርሆዎችና ከቤተ ክርስቲያናችንም ቀኖና ባፈነገጠ መልኩ ከዘመኑ የጎሳ ፖለቲካዊ እሳቤ ጋር የተጣበቁ ሂደቶች እና ድብቅ ውሳኔዎች የቤተ ክርስቲያንን ህልውና የሚገዳደሩ መሆናቸውን ቅዱስ ሲኖዶስ ልብ ሊለው ይገባል። 

ምክንያቱም እንዲህ ያሉ አካሄዶች ለቤተ ክርስቲያናችን ታላቅ የታሪክ ስብራቶች ከመኾናችውም ባሻገር ውሉደ ከህነትንና ሊቃውነተ ቤተክርስቲያንን እንዲሁም ህዝበ ክርስቲያኑን በእጅጉ እያስጨነቁ ያሉ በመኾናቸው ነው። 

ከዚህም አልፎ ሕግ አለበት በሚባል ሀገር ውስጥ ቤተ ክርስቲያናችን ሕጓ ሲጣስና ያለ ቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ ሕገ ወጦች በማን አለብኝነት “ኤጲስ ቆጶሳትን” ሾምን ባሉበት ሰዓት ቅዱስ ሲኖዶስ ባወጣቸው ጥሪዎቸ ኹሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ከልሂቅ እስከ ደቂቅ ጥሪውን ተቀብለን በአነድነት ተገባራዊ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፤ ልዩ ልዩ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ የካህናትና የምእመናን ማኅበራት/ኅብረቶች በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የተሰጠ የጋራ መግለጫ ፪ ፍኖተ ጽድቅ ወሕይወት ጉባኤ ማኅበራ ለቤተ ክርስቲያ ዓለም አቀፍ ኅብረት የሰሜን አሜሪካ ማኅበረ ካህናት የዩኬና አየርላንድ ማኅበረ ካህናት ሞዐ ተዋሕዶ ግብረ ኃይል የነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር በአውሮፓ ስናደርግና በዚህም ጥፋተኞቹ እንዲመለሱና የቤተ ክርስቲያናችን ቀኖናም እንዲከበር ማስቻላችን የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።

 በአንጻሩ ቅዱስ ሲኖዶስ አሁን እየሔደበት ያለው መንገድ ያንን ሕዝበ ክርስቲያኑ በደም መሥዋዕትነት፣ በዕንባና በጸሎት ያስከበረውን ቀኖና በመጣስ ላይ ይገኛል። ከዚህም አልፎ የሊቃውንቱን፣ የማኅበረ ካህናትና ምእመናንን ተደጋጋሚ ጩኸት እንደ ኢምንት ቆጥሮ በማን አለብኝነት ቤተ ክርስቲያናችንን ወደ ጥፋት ጎዳና እየመራት መሆኑ በጣም አስደንጋጭና አሳዛኝ ኩነት ነው። 

በመኾኑም ቤተ ክርስቲያናችን ከላይ ከተጠቀሱት ምስቅልቅል ችግሮች ትድን ዘንድ አሁንም ጊዜው ስላልረፈደ ቅዱስ ሲኖዶስ የሚከተሉትን እርምጃዎች ይወስድ ዘንድ ለመጨረሻ ጊዜ እናሳስባለን፦ 

፩. ቤተ ክርስቲያንን ከከፋ ክፍፍል መታደግ ይቻል ዘንድ በአሁኑ ሰዓት ይፈጸማል የተባለውና ቀኖናን ከመጣስ ባሻገር በውስጡ ፖለቲካዊ ከፋፋይ ሤራ ያጠላበት በመኾኑ ብዙ ሊቃውንትንና ሕዝበ ክርስቲያንን እያስጨነቀ የሚገኘው ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትን ቅዱስ ሲኖዶስ እንዲሠርዝ እንጠይቃለን፤ 

፪. በአጠቃላይ እየታየ ያለውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀኖናዊና አስተዳደራዊ ችግር ከሥር መሠረቱ ማስተካከል ይቻል ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶሱ ባስቸኳይ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሊቃውንት፣ ካህናትና ምእመናንን ያሳተፈ ዓለም አቀፍ ጉባኤ እንዲያዘጋጅና በውጤቱም ዘመኑን የዋጀ አስተዳደራዊ መዋቅር በመዘርጋትና ቀኖናውንም በማስተካከል የቤተ ክርስቲያንን ህልውና እና ልዕልና እንዲያስጠብቅ እንጠይቃለን። 

፫. ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ማድረግ የማይችል ከሆነ፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን ይከበር ዘንድ ቁርጥ ኅሊና ያላቸውን ሊቃነ ጳጳሳት መሪ በማድረግ የሕገ ወጥ ኤጲስቆጶሳት ሹመትን በጥብዓት የምንታገልና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የማስከበር ሃይማኖታዊ ግዴታችንን ለመወጣት የምንገደድ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን። 

፬. ለኤጲስ ቆጶስነት በእጩነት ለተመረጣችሁ መነኮሳት፦ ምንም እንኳ ሹመቱ ሊገባችሁ የምትችሉ ብትኖሩም ይህ ሹመት ያለ ጊዜውና ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ የመጣና ከመንፈሳዊነቱ ይልቅ ፖለቲካዊ ተልዕኮ ያለበት መሆኑን ተገንዝባችሁ እጩነቱን ባለመቀበል ራሳችሁን እንድታገልሉና ቤተ ክርስቲያናችሁን ከከፋ አደጋ እንድትታደጉ እናሳስባለን። 

ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ. ም.

 ፩. የሰሜን አሜሪካ ማኅበረ ካህናት 

፪. የዩኬና አየርላንድ ማኅበረ ካህናት 

፫. የነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር በአውሮፓ 

፬. ሞዐ ተዋሕዶ ግብረ ኃይል 

፭. ፍኖተ ጽድቅ ወሕይወት፣ ጉባኤ ማኅበራ ለቤተ ክርስቲያን፣ ዓለም አቀፍ ኅብረ 

Cover letter-EOTCCPA PR 040823.pdf

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን ኅብረት የአቋም መግለጫ 

ሰኔ ፳ ፩ ቀን ፳ ፻ ፲ ፭ ዓ.ም 

EOTCCPA-RE20151021 

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን ኅብረት የአቋም መግለጫ

 “በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!” 

“በእናንተ ዘንድ ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ።” 1ጴጥ 5፡2 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ለማጥፋት ለዘመናት ሲታለም የኖረውን ዕቅድ እውን ለማድረግ ጊዜው አሁን ነው በሚል ቤተ ክርስቲያንን ቀኖናዋን በማፍርስ ለጊዜው በፖለቲካ ቁጥጥር ሥር እንድትወድቅ፣ በኋላ ደግሞ ለመበታተን ታስቦ በፖለቲከኞች የተጠነሰሰውን ሃሳብ ለመተግበር እንዲመች የዘር ሃረግን ወይም ጎሳን መሰረት በማድረግ ኤጲስ ቆቦሳትን ለመሾም ቅዱስ ኢኖዶስ አስመራጭ ኮሚቴ ሰይሞ የምርጫ ቀንን እየጠበቀ ነው።ይህ አካሄድ ሐዋርያዊት ብለን የምናምንባትን ቤተ ክርስቲያን የፖለቲካ ሃሳብ ማስፈጸሚያ ከማድረግ አልፎ ቤተ ክርስቲያኒቱን እና ሃገራችንን የሚያጠፋ አካሄድ ጅምር ነው።ስለሆነም የሰሜን አሜሪካ የካህናትና የምእመናን ኅብረት ይህንን የመለካውያንን አካሄድ በጽኑ የሚያውግዝ ሲሆን፣ ቅዱስ ሲኖዶስም ነገሩን በጥሞና በመከለስ የዛሬን ሳይሆን በቀጣይ ዘመናት በሃገሪቱና በቤተ ክርስቲያን ላይ ሊደርስ የሚችለውን የከፋ አደጋ በመመልከት ውሳኔውን በመከለስ ሹመቱን እንዲያስቆም በመጠየቅ ዙርያ ባለ ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል፦ 

የአቋም መግለጫ 

1. ቅዱስ ሲኖዶስ ግንቦት ፲ ፬፡፳ ፻ ፲ ፭ ዓ.ም ባደረገው ምልአተ ጉባዔ ላይ በፖለቲካ ተጽዕኖና በግለኞች የውስጥ ጫና፣ ጎሳን ማዕከል ባደረገ መልኩ ኤጲስ ቆጶሳትን ለመሾም መወሰኑ ይታወሳል። በእርግጥም የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብጹአን አባቶች ቤተ ክርስቲያን ዘር ተኮር አካሄድ መሄድ እንደሌለባት ሳይገነዘቡ ቀርቶ  ሳይሆን የአላውያንን ጫናና የመለካውያንን ዛቻ ካለመቋቋ የተነሳ የተወሰደ ውሳኔ እንደሆነ ማንም የሚረዳው ጉዳይ ነው። ሆኖም ይህ ጎሳን መሠረት ያደረግ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት በአጭር ጊዜ ውስጥ ካልቆመ በቀጣይ በዘር ፖለቲካ ተደራጅቶ ሕዝብን ሲያፋጅ የኖረው ብሔር ተኮር የሃገር አስተዳደር ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ በመግባት ቤት ክርስቲያንን ለተመሳሳይ አደጋ ያጋልጣታል።ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን የሹመት ውሳኔ ሲያስትላልፍ የቤተ ክርስቲያኒቱን የአጭር ጊዜ ብሎም የረጅም ጊዜ አደጋዎችን በበቂ ሁኔታ ከግንዛቤ ያስገባ አይመስልም። ምክንያቱም እኒህ የአጭር ጊዜና የረጅም ጊዜ አደጋዎች ከግንዛቤ ገብተው ቢሆን ኖሮ ብጹ አን አባቶች እንዲህ አይነቱን አደጋ አዘል ውሳኔ እንድማይወስኑ በአባቶቻችን እንተማመናለን። አሁንም በግንቦቱ ምልአተ ጉባዔ የተወሰነው ዘር ተኮር የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ኢቀኖናዊ በሐዋርያት ኋላም በቅዱሳን ሐዋርያት እግር ተተክተው ቤተ ክርስቲያንን ያገለገሉ አባቶች አስተምህሮና የክርስትና ሕይወት ውስጥ ያልታየ አዲስ ትንግርት ነው። ጉዳቱም ግልጽ ነው። 

ቤተ ክርስቲያኒቱን ከአንድነት ወደ ብዙህነት በመበትን የፖለቲከኞችና ለዘመናት ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመውረስና የክህደት ትምህርትን ለማስፋፋት የሚቋምጡት የመናፍቃን መናኸሪያ የሚያደርግ መሆኑ የተሰወረ አይደለም። በተመሳሳይ በሃገሪቱ ያለው የዘር መራሽ አስተዳደር ሁኔታ በቤተ ክርስቲያን ደረጃ በመውረድ በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገር ያለችውን ቤተ ክርስቲያን በተመሳሳይ ሁኔታ በዘር እርስ በርስ እንዲከፋፈል፣ እንዲጣላ ብሎም ትውልዱን ወደ ማይመለስበት የጥፋት አዘቅት ውስጥ እንደሚከት፣ የመእመናንንም ሕይወት ፈጽሞ የሚያበልሽና አላስፈላጊ የዘር ግጭትን የሚያስነሳ ይሆናል። አልፎ ተርፎ ሃገርን አንድ አድርጋ የነበርች ቤተ ክርስቲያን በዘር ስትበተን ሃገርም አብሮ ይበተናል።ለዚህ ደግሞ በር ከፋች የሆንነው የዚህች ቅድስት ቤት ክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ በተለይም የቤተ ክርስቲያኒቱ ዋና መሪ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ በእግዚአብሔርም ሆነ በሰው ዘንድ ፤ በደካማ አድራጎታችን በታሪክ ስንዘከር እንኖራልን።

በመሆኑም ቅዱስ ሲኖዶስ እኒህን ጉዳዮች በመመልከት በመጪው ሐምሌ ፱፡፳ ፩ ፲ ፭ ዓ.ም ሊያደርግ ያቀደውን የትውልድ ሃረግን መሠረት ያደረገ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት በመተው፤ ወደ ፊት የቤተ ክርስቲያኒቱን መሠረታዊ ችግር ብሎም እየደረስበባት ያለውን ፖለቲካዊ ትጽዕኖ በማጤንና ከላይ የተጠቀሱትን መጻኢ አደጋዎች ከግንዛቤ በማስገባትና መፍትሄ በመስጠት፣ ተከትሎም ዘርን ማዕከል ያላደረገ ሹመትን ወደ ፊት በማድረግ የቤተ ክርስቲያንን አንድነትና ኅብረትን ማምጣት ያስፈልጋል። ስለሆነም የሰሜን አሜሪካ የካህናትና የምእመናን ኅብረት(ካምኅ) ቅዱስ ሲኖዶስ በመጪው ሐምሌ ፱፡ ፳ ፩ ፲ ፭ ዓ.ም ሊያደርግ ያቀደውን ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ሰኔ ፳ ፭፡ ፳ ፻ ፲ ፭ ዓ.ም በተጠራው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባዔ ላይ በመወያየት እንዲያራዝም ቢደረግና ቀድሞ ሊተገበር በሚገባው የቤተ ክርስቲያን አንድነት ጉዳይ ላይ ቅድሚያ እንዲሰጥ አባቶቻችንን በታላቅ አክብሮት እንጠይቃላን። 

2. ቀደም ብሎ ቅዱስ ሲኖዶስ የኤጲስ ቆጶሳትን አመራረጥና አስተዳደራዊ አካሄዶችን የሚያጠና “በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ የተቋቋ ዐቢይ ኮሚቴ’ በመባል ተስይሞ የሚሰራ ስብስብ ተመስርቶ እንደነበር ይታወሳል። ይህ ዐቢይ ኮሚቴ አባቶችንና በተለየዩ የሙያ ዘርፎች የሚገኙ የቤተ ክርስቲያን ልጆችን ያካተተ ነው። ይህም ይህም ዐቢይ ኮሚቴ ተገቢውን ጥናት አድርጎ ለቅዱስ ሲኖዶስ የኤጲስ ቆጶሳት ሲመት የአመራረጥ ሂደቶችን የሚጠቁም የምርጫ መስፈርት ሰንድ ለጠቅላይ ቤተክህነት እና ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት አስገብቶአል፤ ሆኖም ግን ይህ ወሳኝ ጥናት በምልዐተ ጉባኤው እንዳይጸድቅ ወደ ጎን አድርጎታን። ስለሆነም ይህ ኮሚቴ ያቀረበው የአሰራር ዘይቤ በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርምሮ የሚታረመው ታርሞ፣ ሥራ ላይ ቢውል ቤተ ክርስቲያንን በእጅጉ ይጠቅማል ለአሽሚ ጉዳዮችም መፍትሄ ይሆናል ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን በምሁራኑ የቀረበውን ጥናት አስፈላጊውን እርማት በማድረግ ተግባር ላይ እንዲያውለው በታላቅ ተህትና ሃሳባችንን እንለግሳለን። 3. በትግራይ ክልል ያሉ ብጹአን አባቶች ከዋናው የቅዱስ ሲኖዶስ፤ ለራሳቸው “የእናቴ መቀነት አደናቀፈኝ” መሰል፤ ምክንያት በመፍጠር ራሳቸውን አግልለው የትግራይ ኤጲስ ቆጶሳትን እንሾማለን በማለት ቤተ ክርስቲያንን ወደ ከፋ አዘቅት ውስጥ ሊከቷት በትጋት እየተንቀሳቀሱ መሆኑ የአደባባይ ምሥጢር ነው።

 ይህ ነገር በአስቸኳይ የጋራ መፍትሄ ተፈልጎለት ካልቆመ ከላይ ተራ ቁጥር 1 ላይ የገለጽናቸው አደጋዎች እንዲከሰቱ በእጅጉ የሚያፋጥ ነው። ከዛም በዘለለ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከአንድ የኢትዮጵያ አንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ወደ ክልል ደረጃ ሲኖዶስ በመከፋፈል ለማክሰም የተፋጠነ ይሆናል። ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ እነዚህን የትግራይ ሊቃነ ጳጳሳት ጊዜ ሳይወሰድ በማነጋገር ወደ አንድነት እንዲመጡ ከፍተኛ ጥረት እንዲያደርግ እንጠይቃለን። 

4. በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት መካከል ከመንግሥት ጋር ቀጥተኛም ሆነ በተዘዋዋሪ ከመንግሥት ጋር ትስስር ያላቸውና ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ይልቅ የመንግሥትን ቃል ፈጻሚዎች ፤ከእግዚብሔር ይልቅ መንግሥትን ማስደሰት ተግባራቸው የሆነ ሊቃነ ጳጳሳት መኖራቸው እሙን ነው፣ይህ ዐይነቱ ማንነት የቅዱስ ሲኖዶሱን አንድነት የሚንድ ሲሆን ለግለሰቦቹም ሆነ ለቤተ ክርስቲያን ብሎም ለሃገሪቱ ጎጂ ስለሆነ፤ በዚህ አይነቱ ተግባራት ላይ የተሰማሩትን ብጹአን አባቶችን ቅዱስ ሲኖዶስ በመወ ያየት የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስድ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን። 

5. የቅዱስ ሲኖዶስ ስሙና ግብሩ አንድ ሊሆን ይገባል። ስለሆነም ብጹአን አባቶች ለእውነት ቆመው እውነትን ተናግረው ዘረኝነትን፣ጎጠኝነትን፣ ከፋፋይነትን በማውገዝ ከፖለቲካ ተጽአኖ ነጻ የሆነ ጉባኤ እንዲኖረን ሊሰራበት ይገባል፣ ስልሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ ዘረኝነትን፣ጎጠኝነትን፣ ከፋፋይነትን እንዲያወግዝና ለእነዚህ የስጋ ፍሬዎች መፈልፈያ የሆኑትንም ለይቶ እንዲያወጣ ስንል እንጠይቃለን። 

6. ዛሬ ብዙ ምእመናን በእናንተ በአባቶቻችን የአስተዳደር አካሄድ እንዲሁም የአቋም መዋዠቅ አልፎ ተርፎ ገዳማት በጦር መሣርያ ሲደበደቡ፣ ለቁጥር አታካች የሆኑ መነኮሳት ሲገደሉ፣ ስለቤተ ክርስቲያን ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ ካህናት ና ምእመናን ሲገደሉ፣ አካላዊና ስነ ልቦናዊ ጥቃት ሲደርስባቸው፣ ሲታሰሩ ከሥራ ገበታቸው ላይ ሲፈናቀሉ ሃገር ስትበተን ዜጎች ከቤት ተፈናቅለው በሜዳ ሲጣሉ በጠራራ ፀሐይ ልጆቻቸው በጅብ ሲበሉ ፍትህ ተጓድሎ እንባ በሜዳ ሲፈስ። ቤተ ክርስቲያን አይታ እንዳላየ ሰምታ እንዳልሰማ በመሆኗ እና ከእግዚአብሔር የተሰጣችሁን የእረኝነት ኃላፊነት ሳትወጡ የተዘረዘሩትን ጉዳዮች ወደጎን ችላ በማለት ዝምታን በመምረጣችሁ የአእላፋት ምእመናንን ልብ ተሰብሮ በሃዘን ውስጥ ይገኛሉ ”ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ ሕያው ነኝና እረኛ ስለሌለ እረኞቼም በጎቼን ስላልፈለጉ እረኞችም ራሳቸውን እንጂ በጎቼን ስላላሰማሩ፥ በጎቼ ንጥቂያ ሆነዋልና፥ በጎቼም ለምድር አራዊት ሁሉ መብል ሆነዋልና” ሕዝ 34፡8። አልፎ ተርፎ በእጃቸው የክርስቲያንን ደም ያፈሰሱ/ ያስፈሰሱ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ስልጥፋታቸው ሳይጠየቁ ወደአገልግሎት መሰማራታቸው በምእመናን ሕይወት ላይ መሳለቅ ነው። ስለሆነም ቅዱስ ፓትርያሪኩና እናንተ ብጹአን አባቶቻችን ይህንን ዝምታ በመስበር ያለመሰልቸት ቤተ ክርስቲያን መከራ ስትቀበል መነኮሳት መከራ ሲደርስባቸው ፍትህ ሲጓደል አገልጋዮች ና ምእመናን ሲጎሳቆሉ ያለመሰልቸትና ያለመታከት በየጊዜው እውነትን በመናገር የአማናዊውን ኖላዊ፣ የክርስቶስን ባህርይ በማንጸባረቅ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ በታላቅ ትህትና በልጅነት መንፈስ ልናስታውስ እንወዳለን።  

 7. በመጨረሻም በጥር ወር በተካሄደው የቤተ ክርስቲያን ግርግርን ተከትሎ ብዙ ሊቃነ ጳጳሳት ከሃገረስብከታቸው ተፈናቅለው፣ በየሃገረ ስብከቱ የሚገኙ አገልጋዮችም መከራ ጸንቶባቸው ስራቸውን እንዳይሰሩ ተደርጎ በመንግስት ባለስልጣናት ተጸኖ እየደረሰባቸው ነው።ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ ከሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በመነጋገር ብጹአን አባቶች ወደየ ሃገረ ስብከታቸው በመመለስ አገልግት መስጠት እንዲጀምሩ እንዲሁም በየሃገረ ስብከቱ የሚገኙ አገልጋዮች ይህም የቤተ ክርስቲያንን አገልጋዮች በነጻነት የተጣለባቸውን መንፈሳዊ ሃናፊነት እንዲወጡ ቅዱስ ሲኖዶሱ ትኩረት እንዲሰጠው በልጅነት መንፈስ ሃሳባችንን እንለግሳለን። 

ወስብሐት ለእግዚአብሔር 

ዋሺንግተን ዲሲ ሰኔ 21 ቀን 2015 ዓ.ም

 (June 28, 2023) 

EOTCCPA Press Release 0521.pdf

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን ኅብረት የአቋም መግለጫ

ግንቦት ፲ ፫ ቀን ፳ ፻ ፲ ፭ ዓ.ም

EOTCCPA-RE20150913

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን ኅብረት የአቋም መግለጫ


“በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!”

“በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።” ሐዋ 20፡28


በመንግሥት ጣልቃ ገብነት እና አቀናባሪነት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ በጥር ወር የተከሰተው የሕገ ወጥ ሹመት ችግሩ ያ ያልተቀረፈ ከመሆኑም ባለፈ መንግሥት ስልቱን በመቀያየር ያቀደውን ትልም ለማስፈጸም በትጋት እየሰራ ይገኛል።

አሁንም መንግሥት በቀጥታ ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት መካከል ለራሱ አጀንዳ አስፈጻሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሊቃነ ጳጳሳትን በመመልመል ዓላማውን ለማስፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስን የመክፈል ሥራ እየሠራ መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው። ለዚህም ዐቢይ ማሳያው በቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ የርክበ ካህናት ስብሰባ ላይ

“ሊቃነ ጳጳሳት ለአንድ ብሔር ብቻ” ይሾሙ በማለት መንፈሳዊነት የሌለው፤ ከሐዋርያት አስተምህሮና ቀኖና ውጭ ለተግባራዊነቱም ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተካሄደ መሆኑ ነው። 

ይህ አካሄድ ሐዋርያዊት ብለን የምናምንባትን ቤተ ክርስቲያን የፖለቲካ ሃሳብ ማስፈጸሚያ ከማድረግ አልፎ ቤተ ክርስቲያኒቱን እና ሃገራችንን የሚያጠፋ አካሄድ ጅምር ነው።ስለሆነም የሰሜን አሜሪካ የካህናትና የምእመናን ኅብረት ይህንን የመለካውያን አካሄድ በጽኑ የሚያውግዝ ሲሆን፣ መንግሥት ቤተ ክርስቲያኒቱ በሰላም እንዳትተዳደር በቅዱስ ሲኖዶስ መንፈሳዊ አስተዳድር ውስጥ ጣልቃ በመግባት፣

አገልጋይ ካህናቷን፣ ሊቃውንቷን እና ምእመናኗን በመግደል፣ በማሰር እና በማሰቃየት መከራ እያጸናባት ሲሆን የመጨራሻ ግቡም ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ከምድሪቱ ላይ ማጥፋት ብሎም ኢትዮጵያ የምትባል ሃገርን መበተን ነው።

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ እንዲሁም አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ቤተ ክርስቲያን ከተመሰረትችበት ጊዜ ጀምሮ በውስጥ በመናፍቃን እና ለዚህ ዓለም ባደሩ ምንደኞች፤ በውጭ ደግሞ በአላውያን ነገሥታት ስትፈተን የኖርች ወደ ፊትም በፈተና ውስጥ የምትኖር ናት። ሆኖም በየዘመናቱ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያንን ይመሩ ዘንድ ጳጳሳት አድርጎ የሾማቸው ቀደምት አበው “ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል” በማለት የአላውያንን እና የሰንፎችን ትእዛዝ ወደ ጎን በመተው ራሳቸውን በሰማእትነት አሳልፈው በመስጠት ይህችን ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዘምን ለተገኘነው አስረክበዋል።

ሁላችሁም እንደምታሳትውሱት ዛሬ ቤተ ክርስቲያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተከፋፍላ አንድነቷን አጥታ የተለያየችው በ451 ዓ.ም በኬልቄዶኑን ጉባኤ መለካውያን የሊዮንን ትእዛዝ በማስፈጸማቸው ነው። በዚህ ጉባኤ እነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ መከራን ተቀብለው መከራቸው የሃይማኖት ፍሬአቸው እንደሆነ በማመን “ዝንቱ ውእቱ ፍሬ ሃይማኖት” በማለት በመጽናታቸው ቅድስቲቱ ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊ ተዋረድን ጠብቃ እንድትኖር የብኩላቸውን መስዋእትነት በመክፈል መንፈሳዊ ተጋድሎን ፈጽመዋል። ብፁዓን አባቶች እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ፤ምናልባትም እግዚአብሔር እንደ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ በእውነት መሠረት ላይ በመቆም የዚህችን ንጽህት ቤተ ክርስቲያን አንድነት እንድትጠብቁና ዋጋ እንድትከፍሉ በመንበሩ ተቀምጣችኋል። እድሉን ሰጥቶአችሁ እንደሆነ ማን ያውቃል። እድሉን ተጠቅማችሁ ይህችን ቤተክርስቲያን ብታድኑ ሃገራችሁን ብሎም ትውልዱን አዳናችሁ ማለት ነው። ታሪካችሁም በሰማይም በምድርም በቀለመ ወርቅ ተጽፎ ይኖራል። ነገር ግን አላውያንን በመፍራት ቤተ ክርስቲያንን የሚያጠፋ ጥቁር የታሪክ አሻራ ካኖራችሁ በሰማይም በምድርም ታሪካችሁ ተበልሽቶ በታሪክ ስትወቀሱ ትኖራላችሁ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ኅብረት በቤተ ክርስቲያን ላይ እየተደረገ ያለውን እያንዳንዱን ተጽእኖ በአትኩሮት እየተከታተል ሲሆን ከላይ ያነሳነው ብሔር ተኮር እካሂድን አስመልክቶ እና በመሰል ጉድዮች ዙርያ በተደጋጋሚ የአቋም መግለጫዎችን ስናወጣ የቆየን ሲሆን አሁንም በተፈጠረው የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ዙርያ ኅብረቱ የሚከተለውን ባለ 4 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል፦

የአቋም መግለጫ

1- በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ መልኩ “ለአንድ ብሔር ብቻ” “ከአንድ ብሔር ብቻ” ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ የቀረበው አጀንዳ እጅግ ልብ ሰባሪ ከመሆኑ ባሻገር ቤተ ክርስቲያኒቱ የክርስቶስን ወንጌል የማትሰብክ፤ ከአምላኳ ይልቅ ለአላውያኑ ታዛዥ አድርጎ እንድትታይ የሚያሳይ ገጽታን የሚፈጥር ሆኖ አግኝተነዋል። ከላይ በመግቢያችን ላይ እንደጠቀስነው የሊዮንን ሃሳብ ሊያስተገብሩ በሞከሩ ግለሰቦች ምክንያት “ጉባኤ ከለባት” ተብሎ የቀረው የኬልቄዶኑ ጉባኤ ዛሬ ዓለም ላለበት የተፋለሰ እምነት መሰረት ጥሎለታል። አላውያን ያልፋሉ ነገር ግን እነሱን ደስ ለማሰኘት ወይንም የተሸከሙትን የጦር መሣሪያ በመፍራት ቤተ ክርስቲያንን የማይሆን አዘቅት ውስጥ መወርወር፣ ኃላፊነት የጎደለው አካሄድ ከመሆኑም ባሻገር በታሪክ የማይረሳ ጠባሳን መጣል ነው።

ሐዋርያትም “ከሰው ይልቅ እግዚአብሔርን ደስ ልናሰኝ ይገባል” በማለት ለእግዚአብሔር በመታዘዝ ሃይማኖትን አጽንተዋል። በመሆኑም በዘመናት የማይለወጠውን እግዚአብሔርን ደስ እናሰኘው። እኛ ክርስቲያኖች አግልግሎታችንም ሆነ ሹመታችን እንደ ብሉይ ኪዳን በዘር ሐረግ ሳይሆን በጥምቀት “ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤

እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም” ከቅድስት ሥላሴ በመወለድ ባገኘነው ልጅነት እና ከክርስቶስ ጋር ባለን ኅብረት ነው። ስለሆነም በእናንተ መካከል የዘረኝነትን ሃሳብ ያመጣውን አባት እንዲታረም ግስጻችሁ፤ “ከአንድ ብሔር ብቻ ፤ለአንድ ብሔር ብቻ” የሚለውን የአሿሿም አካሄድ ከእኛ ከልጆቻችሁ ጋር በአንድነት በመሆን እንድታወግዙት ብሎም ነቅላችሁ እንድትጥሉት በቤተ ክርስቲያን አምላክ ስም እንጠይቃለን። ይልቁንም ታሪካችሁ በቀለመ ወርቅ የሚጻፍበትን እና ለቤተ ክርስቲያን በዘላቂነት የሚጠቅም ከዘረኝነት የጸዳ፤ በእውነት ላይ የተመሰረተ አሰራርን ትተክሉ ዘንድ በትህትና እንጠይቃለን።

2- ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት የቤተ ክርስትያንን ጥያቄ ብቻ ሊመልስ የሚችል እና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንና ቀኖና በጠበቀ መልኩ መደረግ አለበት ብሎ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ኅብረት እንዲሁም መላው ህዝበ ክርስቲያን ያምናል። ስለሆነም ሲመቱ ቤተ ክርስቲያን በየሃገረ ስብከቱ ያለውን ክፍተትን በመጥናት፣ ተደርበው የተያዙ ሃገረ ስብከቶችን ለአገልግሎት ቅልጥፍና በሚረዳ መልኩ ለማከፋፈል እና የስራጫናን ለመቀነስ ብሎም ተመሳሳይ መንፈስዊ እገልግሎቶችን ታሳቢ በማድረግ መሾም የሚገባ ሲሆን። በዚህም ውስጥ ሊካተቱ የሚገባቸውን በሃይማኖት የጸኑትን በምግባራቸው አርአያ ክህነት ያላቸውን ለመንጋው የሚራሩና መልካም እረኛ ሊሆኑ የሚጋባቸውን ቤተ ክርስቲያን ባወጣችው መመርያ መሠረት ብቻ መስፈርቱን የሚያሟሉትን ሊሆን ይገባል እንጂ የዘር ኮታን መሰረት ያደረገን ሊሆን አይገባም።

3- በዚህ ወቅት በመንግሥት ጫና የቅዱስ ሲኖዶሱን አባላት አቋም በመከፋፈል ሲመተ ኤጴስ ቆጶሳት ተግባራዊ ከተደረገ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ሉዓላዊት፣ ኩላዊትት፣ ቅድስትና አንዲት መሆኑዋን ቀርቶ ሁለት እና ከዚያ በላይ ሲኖዶስ፣ ሁለት እና ከዚያ በላይ ፖትርያርክ የተወሰነ ጎሳ ብሔረሰብ ወኪሎች የፌዴሬሽን የጳጳሳት ምክር ቤት፣ ጥገኛ እና መለካዊት፣ የተከፋፈለች በስም ብቻ የምትጠራ ቤተክርያን በመፍጠር በመንፈሣዊ መሪዎቿ እና ተከታዮቿ ምዕመናን መካከል ልዩነት በመፍጠር የጦርነት አውድማ አበጅቶ ሲናቆር ኦርቶዶክሳዊን ማጥፉትና ሀገረ ኢትዮጵያን ማፍረስ ነው፣ የታሪክ ጠባሳ እንዳይፈጠር ፣ሁሉም አባቶች እውነትን ይዘው አቋማቸውን በአንድነት በማሳውቅ ከውስጥም ሆነ ከውጭ ያሉ አጽራረ ቤተ ክርስቲያናት እና ፖለቲካው ጭምር ያጠመደውን  የሴራ ወጥመድ ሰባብረው በመጣል ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን ላልተወሰነ ጊዜ በማራዘም ትውልዱን ከነፍስ ከስጋ ጥፋት እንድትታደጉ እንማጸናለን።

4- የሃገሪቱ የፌደራል መንግሥት ብሎም የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ያለ አግባብ በቤተ ክርስቲያኒቱ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ላይ ግልጽ ጣልቃ ገብነትን እያሳየ የእምነትን ነጻነት እየተጋፋ መሆኑ ይታወቃል። ከላይ እንደተጠቀሰው በጥር ወር በተካሄደው ሕገ ወጥ ሹመት ባስከተለው ሁከት ምክንያት ብዙ የእምነቱ ተከታዮች እና አገልጋዮች የሕይወት መጥፋት፣ የአካል መጉደል፣ እስራት እና እንግልት ደርሶባቸዋል እያደረሰባቸውም ነው። ከዚህ በፊት በጠየቅነው መሠረት የመንግሥት አካላት የጉዳዩ አቀናባሪዎች በመሆናቸው ጥፋቱን ባደረሱት አካላት ላይ ምንም አይነት የሕግ ተጠያቂነት ያላደረጉ ከመሆኑ ባለፈ ሕገ ወጥ ተሿሚዎቹ ዛሬም ድረስ ቤተ ክርስቲያንን እያወኳት ነው። 

ከዚህም ባሻገር በተለያዩ የትግራይ ከዚህም ባሻገር በተለያዩ የትግራይ ሃገረ ስብከቶች የሚገኙ ሊቃነ ጳጳሳት ደግሞ ግንባር በመፍጠር “መንበረ ሰላማ” በሚል ስያሜ “የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነትን” (መሥርተናል ከማለት) አልፎ ተርፎ ያለ ቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ከሃገር ውጭ ያሉ አህጉራትን በመከፋፈል ራሳቸውን የተለያዩ አህጉረ  ስብከቶች ሊቃነ ጳጳሳት አድርገው መሾማቸው እና ከቤተ ክርስቲያኒቱ አንድነት የተለየ አካሄድ መከተላቸው እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ይህ ችግር ሳይፈታና እንድነት ሳይመጣ ሹመት ማስቀደሙ ከድጡ ወድ ማጡ ከመሸጋገር ውጭ ቤተ ክርስቲያንን አይጠቅምም። በሌላ እንጻር አሁን እየትካሄደ ባለው የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ ገና ከጅምሩ ሹመቱ ዘር ተኮር እንዲሆን በመንግሥት የተሰጠውን ቀጭን ትእዛዝ ለማስፈጸም በሚደረገው ውክቢያ ቤተ ክርስቲያን የከበደ ፈተና ውስጥ እያስገባት ነው። በእነዚህና መሰል ምክን ያቶች በዚህ ወቅት ሊደረግ የታሰበው ሹመት፦

ሀ. መንግሥት ሙሉ ለሙሉ እጁን ከቤተ ክርስቲያን ላይ እስኪያነሳ ድረስ፤ 

ለ. በቅዱስ ሲኖዶስም ውስጥ ከዛህም ውጭ ያሉ አባቶች ከዘረኝ ነት አባዜ ወጥተው እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት በመንፈስ ቅዱስ ነገሮችን ማከናወን የሚችሉበትን አመለካከት እስኪያመጡ ድረስ

ሐ. በትግራይ ከሚገኙ አባቶች ጋር በቅርበት አስፈላጊ ውይይት ተደርጎ የቤተ ክርስቲያን አንድነት እስኪጠናከር ድረስ የቅዱስ ሲኖዶስ ትኩረት ከኤጴስ ቆጳሳት ሾመት ይልቅ በሰላም እና የቅዱስ ሲኖዶስ አንድነት ላይ አጥብቆ መስራት ሊሆን ይገባል ብለን እናምናለን። ስለሆነም በአሁኑ ወቅት ሊከናወን የታቀደው የኤጴስ ቆጳሳት ሹመት ከዚህ በላይ (ሀ-ሐ) የዘረዘርናቸው ነገሮች እስኪሟሉ ድረስ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም በአጽኖት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ኅብረት አጥብቆ ይጠይቃል።

ኅብረቱ ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ እያደረገ ያለውና በቀጣይ ሊያደርግ ያቀደው ተግባራት

1- መንግሥት በቤተ ክርስቲያን ላይ ብሎም በንጹሃን ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለው በደል የከፋ ከመሆኑ ባሻገር ይህ ተጽ እኖ የቤተክርስቲያንን ህልውና አደጋ ፤ላይ የሚጥል ነው ስለሆነም ጉዳዩን ለዐለም ማህበረሰብ ለማሳወቅ በቅርቡ ዐለም አቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ የምንጠራ ይሆናል።

2- መንግሥት ቤተ ክርስቲያንን በመከፋፈል ሃይማኖትን የማጥፋት ሃገርንም የመበተን ስራ በከፍተኛ ደረጃ እየሰራ ነው። ይህ ደግሞ በቀጣይነት የማያቋርጥ የእርስ በእርስ ግጭት ፤የደም መፍሰስ እና ግድያ የሚያመጣ፤ ምስራቅ አፍሪካን ብሎም መላው ዓለምን ከፍተኛ ሥጋት ላይ የሚጥል በመሆኑ ይህንን ጉዳይ ለዐለም አቀፍ ተቋማት (የዐለም ባንክ /World Bank፣ የዐለም የገንዘብ ብድር ድርጅት/International Monetary Fund፣ ለአውሮፓ ኅብረት/European Union፣ እና ለመሰል ድርጅቶች) በማሳወቅ ሊደርጉ በሚገባቸው ተግባራት ላይም አብሮ ይመክራል።

3- ከአሜሪካን የሕግ አውጪ አካላት ጋር በሃገሪቱ ባለ ስልጣኖች ላይ የመጓጓዝ ማእቀብ (Travel banning) እንዲጣል ብሎም በዐለም አቀፍ ፍርድ ቤት (International Court) ሃገሪቱ ውስጥ  በመንግሥት እየተካሄደ ላለው ግፍ ግድያ እና እንግልት የመንግሥት ባለስልጣናት እንዲጠየቁ እና ለፍርድ እንዲቀርቡ የማድረግ ሥራው የተጀመረ ሲሆን ይህንኑ ከፍጻሜ ለማድረስ ይሰራል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ዋሺንግተን ዲሲ

ግ ንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም

Cover letter-EOTCCPA PR 040823.pdf

በወቅታዊው የቤተ ክርስቲያን ሁኔታ እና በሃገሪቱ ውስጥ ስላለው የማኅበራዊ ቀውስ ዙርያ የወጣ መግለጫ

ቁጥር፡004/ካምኅ/2015

 ቀን፡ ፴፡ ፳ ፻ ፲ ፭ ዓ.ም ዓ.ም

 April 08 ፣ 2023 

ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት 

አዲስ አበባ 

ጉዳዩ፡ በወቅታዊው የቤተ ክርስቲያን ሁኔታ እና በሃገሪቱ ውስጥ ስላለው የማኅበራዊ ቀውስ ዙርያ የወጣን መግለጫን ስለማቅረብ ይመለከታል

 የተወደዱ ቅዱስ አባታችን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መላው የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ቡራኬያችሁ ትድረሰን እያልን፤ በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው የምንገኝ ካህናት፣ መንፈሳዊ ማኅበራት እና ምዕመናን “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን ኅብረት” በሚል ስያሜ መንፈሳዊ ኅብረትን አቋቁመን፤ በአሜሪካ ሀገር በሕግ ተመዝግቦ እየሠራ ይገኛል። ይህ ተቋም በምንኖርበት አካባቢ፣ በመላው ዩናይትድ ስቴስ ብሎም በዓለም ደረጃ ጉልህ እንቅስቃሴን በማድረግ በቤተ ክርስቲያን እና በተከታይ ምዕመናኖቿ ላይ በዚህ ዘመን በመንግሥት እየተደረገባቸው ያለውን ተጽዕኖ ለመላው ዓለም እያሳወቀ ይገኛል። እንዲሁም ለተለያዩ የመንግሥት አካላት መልዕክትን በማስተላለፍ የቤተ ክርስቲያን አንድነት የሚጠበቅበትን መንገድ በማፈላለግ ረገድ ውጤታማ ሥራን እየሠራ ሲሆን፤ ይህንኑ ተግባር በተጠናከረ መልኩ በትጋት እያከናወነ ይገኛል። ይህ ኅብረት ይዞ የተነሳው ዓላማ ቤተክርስቲያንን ከመንግሥት ተጽዕኖ እንድትላቀቅ፣ ዶግማዊ እና ቀኖናዊ አምልኮቷ ሳይፋለስ ጸንታ ለሚቀጥለው ትውልድ የምትተላለፍበት መንገድ ያለ መታከት ማመቻቸትና ቤተ ክርስቲያን በምትፈልገን ቦታ እና ጊዜ ሁሉ በመገኘት የልጅነት ድርሻችንን ለመወጣት ነው። ኅብረቱ በወቅታዊው የቤተ ክርስቲያን ሁኔታ እና በሃገሪቱ ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ጥናት ካደረገ በኋላ ብዙ ነገሮች እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆናቸውን ተገንዝቧል ። ስለሆነም እነዚህን አሳሳቢ ጉዳዮች አብዛኛዎቹ ቅዱስ ሲኖዶስን ሊመለከቱ የሚችሉ ስለሆኑ፤ ጉዳዮቹን ለእናንተ ለአባቶቻችን በልጅነት መንፈስ ሳንጠቁም ማለፍ እንደሌለብን በመረዳት በአቋም መግለጫ መልክ ያወጣናቸውን ነጥቦች ከዚህ ደብዳቤ ጋር አባሪ አድርገን የላክን ሲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ በመግለጫው የተዘረዘሩት ነጥቦች በጥንቃቄ ቢመረምር እና አስፈላጊውን እርምጃ ቢወስድ ቤተ ክርስቲያንን ከዘለቄታዊ ችግር ሊታደጋት ይችላል ብለን እናምናለን 

ወስብሐት ለእግዚአብሔር 

ርዕሰ ሊቃናት ቀሲስ አብርሃም ሀብተ ሥላሴ ዋና ሰብሳቢ አባሪ፡ 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን ኅብረት ባለ ስድስት ገጽ የአቋም መግለጫ

 ግልባጭ፡ 

o ለቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት o ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዲስ አበባ 

o ለዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ዋሽንግተን ዲሲ 

EOTCCPA Press Release040823 WM_updated.pdf

 በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 

ካህናትና ምዕመናን ኅብረት የጋራ የአቋም መግለጫ 


ሚያዚያ ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓም

EOTCCPA-RE20150801

“በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!”

“በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ።” ኤፌ 4፡3

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ በተከሰተው የጥር 14/ 2015 ዓ.ም ሕገ ወጥ ሹመት፣ የቀኖና እና የአስተዳደር ጥሰት ምክንያት ቤተ ክርስቲያን እስከ አሁን ድረስ በከባድ ፈተና ውስጥ ትገኛለች። ይህንኑ ፈተና የከበደ ያደረገውም ሀገሪቱን የሚያስተዳድረው መንግሥት ነገሩን ማቀናበሩ እና በተለያየ መልኩ ለሕገ ወጥ ቡድኑ ከፍተኛ ድጋፍ በማድረጉ እንደሆነ ከሁሉም ሊሰወር የማይችል ሐቅ ነው። ይህም መንግሥት በሃገሪቱ ውስጥ የአንድ ወገንን የበላይነትን ለማሳየት ካለው ከፍተኛ ጉጉት የተነሳ ቅዱስ ሲኖዶስን በመክፈል ቤተ ክርስቲያኗን መቆጣጠር እንደ አንድ አይነተኛ አማራጭ በመወሰዱ የተነሳ እንደሆነ ይታመናል።

ቤተ ክርስቲያን በመስራቿ በኢየሱስ ክርስቶስ የተጣለባትን መንፈሳዊ ተልዕኮ ለመፈጸም አልፎ ተርፎ ሀገርን ከነሙሉ ክብሯ እና አንድነቷ ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሻገር የምታደርገውን መንፈሳዊ አገልግሎትን ለማሰናከል የተጋረጠባትን ይህን፤ በአይነቱ ለየት ያለ፤ ከባድ ፈተና በዓለም ዙርያ ባሉ ልጆቿ ያላሰለሰ ተጋድሎ እንዲሁም ቤተ ክርስቲያን ለዘመናት ባካበተችው ከፍተኛ የአመራር ብቃት እና በቅዱሳን ጸሎት በመታገዝ፣ የተቃጣባትን እኩይ ተግባር ለጊዜው ጋብ እንዲል ሆኗል።

በስህተት ጎዳና የሄዱት ቆሞሳት ወደ ቤተ ክርስቲያናቸው በይቅርታ እንዲመለሱ ቤተ ክርስቲያን በሯን መክፈቷ እጅግ የሚያስመሰግን ነው። ይህንኑ የቤተ ክርስቲያንንም የሰላም እና የፍቅር ጥሪን በመቀበል ብዙዎቹ ቆሞሳት ወደ እናት ቤተ ክርስቲያናቸው የተመለሱ ቢሆንም አጥፊዎቹ ግን ጥፋታቸውን አምነው “ይቅርታ” ላለማለት የሄዱበት እርቀት እጅግ የሚያሳዝን ሲሆን ዛሬ እነዚህ ሰዎች ወደ ልቦናቸው መመለሳቸው አጠራጣሪ ነው። ሆኖም ግን ቅዱስ ሲኖዶስ በሰፊ ልቦና ስለ ስላም፣ ስለፍቅር እና ሰለቤተ ርስቲያን አንድነት ሲል ግለሰቦቹ ያቀረቡትን ደብዳቤ ተቀብሎ ግዝቱን አንስቶላቸዋል። ይቅርታ ሳይጠይቁ ይቅርታ እንደጠየቁ ተቆጥሮላቸው ያለምንም ቀኖና፤ ግዝት ተነስቶላቸው ወደ እናት ቤተ ክርስቲያን መመለሳቸው ብዙ ካህናትን እና ምእመናንን አስከፍቷል። ይህም ሆኖ ግን ችግሩ ተዳፈነ እንጂ ፈጽሞ አልጠፋም። እንዲያውም ችግሩ መልኩን እየቀያየረ በተለያየ አቅጣጫ ውጥረት እንዲነግስ አድርጎታል። በሕገ ወጥ መልኩ ከተሾሙት ግለሰቦች መካከል አሁንም ወደ ቤተ ክርስቲያን ያልተመለሱ መኖራቸው ችግሩ ሙሉ በሙሉ አለመቀረፉን በግልጽ የሚያሳይ ነው። ይህ ችግር ሳይፈታ በእንቅርት ላይ ጆሮደግፍ እንዲሉ በተለያዩ የትግራይ ሃገረ ስብጀቶች የሚገኙ ሊቃነ ጳጳሳት ደግሞ ግንባር በመፍጠር “መንበረ ሰላማ” በሚል ስያሜ “የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነትን” በመመስረት፤እልፎ ተርፎ ያለቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ከሃገር ውጭ ያሉ አህጉራትን በመከፋፈል ራሳቸውን የተለያዩ አህጉረ ስብከቶች ሊቃነ ጳጳሳት አድርገው መሾማቸው እና ከቤተ ክርስቲያኒቱ አንድነት የተለየ አካሄድ መከተላቸው እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።

ስለሆነም በእነዚህ ዐበይት ችግሮች ላይ፣ በማኅበራዊ ጉዳይ እና ወደ ፊት ስለታሰበው የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ዙርያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ኅብረት የሚከተለውን ባለ 5 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል፦

የአቋም መግለጫ

1. ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ለማስከበር መጋቢት 6 /2015 ዓ.ም. ባካሄደው ምልዓተ ጉባኤ ያወጣው ባለ ስድስት ነጥብ የአቋም መግለጫ መሰረት በማድረግ እና ይህንኑ የቅዱስ ሲኖዶስን የፍቅር ጥሪ በመቀበል ከዚህ በፊት በሕገ ወጥ መንገድ ተሹመናል ይሉ የነበሩ ቆሞሳት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መመለሳቸው እጅግ መልካም ነገር ሆኖ ብናገኘውም ቆሞሳቱ ለቅዱስ ሲኖዶስ ያስገቡት “የተመልሰናል” ደብዳቤ ግን ፍጹም መንፈሳዊ ይዘት የሌለው፤ ይልቁንም ከቤተ ክርስቲያኗ ጥሪ ይልቅ በመንግሥት በኩል የቀረበውን ሐሳብ መሠረት ያደረገ ነው። የገባውንም ደብዳቤ አስከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ውግዘቱን ያለ ምንም ዓይነት ቀኖናዊ ሥርዓት ማንሳቱ ከቤተ ክርስቲያኗ የንስሐ ትምህርት አንጻር አስተማሪ ሆኖ አላገኘነውም። ምዕመናን እግዚአብሔርን በድለናል ብለው ንስሐ ሲገቡ አባቶች የሚሰጡት ቀኖና በቤተ ክርስቲያናችን የኖረ፣ በፍትሐ ነገሥቱም ተሰፍሮ፣ ተቆጥሮ የተቀመጠ ፤ከአምላካችንም የታዘዝነው የአምልኮት ሥርዓት ሆኖ ሳለ፤ በአደባባይ ለተሠራ በደል ግን ምንም ዓይነት ቀኖና ሳይሰጥ ውግዘቱን ማንሳት በአማኝ ክርስቲያኑ ዘንድ አምላካችን መድኃኒታችን፤ ኢየሱስ ክርስቶስ የሠራውን የንስሐ ቀኖና እንደተጣሰ ሊታይ እና የምዕመናን መንፈሳዊ ሕይወት በእጅጉ አደጋ ላይ የሚጥል፣ በቤተ ክርስቲያኗ አስተምህሮ ላይ ጥርጣሬን የሚያሰርጽ፣ ብሎም ያለ ቀኖና እንደ ልብ መኖር እንደሚቻል እንዲቆጠር የሚያደርግ ሲሆን፤ ከዚህም ባሻገር በእኛ እይታ የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልናን የሚጎዳ ይሆናል። ብዙዎቻችን እንደምናስታውሰው በ1980ዎቹ መጨረ ገደማ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሃይማኖትን እና ስርአት እናድሳለን በማለት በተሃድሶ እንቅስቃሴ ውስጥ ያገኘቻቸውን አገልጋይ ካህናትን በአደባባይ ንስሃ እንዲገቡ አድርጋ ቀኖና ሰጥታ ወደ የገዳማቱ በመላክ፣ በተላኩበት ገዳማትም በመቆየት የታዘዙትን ቀኖና እንዲፈጽሙ ማድረጓ የሚታወስ ነው። ይሁን እንጂ አሁን ተመልሰናል ባሉት ሊቃነ ጳጳሳት እና ቆሞሳት አባቶች ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ ተመሳሳይ አይነት አሰራርን አለመከተሉ እና ቀኖና ሳይሰጥ፤ ቀኖናውም ሳይፈጸም ውግዘቱን ማንሳቱ፣ ከቤተ ክርስትያኗ አስተምህሮ አንጻር መንገድ የሳተ እና ለምዕመናን መንፈሳዊ ሕይወት አሰናካይ መሆኑ ግልጽ ነው። ስለሆነም የቤተ ክርስቲያኗን ልዕልና ከማስከበር አንጻር፣ አስተምህሮዋንም በተግባር ከማሳየት አንጻር፣ ብሎም ለምዕመናን ሕይወት ጥንቃቄ ከማድረግ አንጻር እንደ ቤተ ክርስቲያን ልጅነታችን፤ ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን እርማት ቢያደርግ መልካም እንደሚሆን ልንጠቁም እንወዳለን።

2. በመጪው የግንቦት ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳትን ለመሾም ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ይህ ጉዳይ አስፈላጊ እና ወደ ፊትም አገልግሎትን በምልዓት ለማዳረስ እንደሚረዳ የታወቀ እውነታ ነው። ነገር ግን በአሁኑ ሰዐት በትግራይ ያሉ ጳጳሳት የራሳችን መንበር፤ “መንበረ ሰላማ” ፤በሚል “የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት” አቋቁመናል፣ ከማዕከላዊው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጋርም ግንኙነት የለንም በማለት በተደጋጋሚ መግለጫ ማውጣታቸው ይታወቃል። ይህ ጉዳይም ቤተ ክርስቲያንን እና መላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዕመናንን ልብ ያሳዘነ ፣ቅስምንም የሰበረ ነው። ቅዱስ ሲኖዶስም ነገሩን በትኩረት በማየት በእነሱ በኩል ለቀረቡት መግለጫዎች ተገቢውን መልስ በመግለጫ መልኩ ሰጥቷል፤በተለያዩ ጊዜያትም የሰላም ጥሪን በደብዳቤ አስተላልፎአል፤ ይህም ቅዱስ ሲኖዶስን የሚያስመሰግን ነው። ይሁን እንጂ ችግሩ በደብዳቤ መላላክ እና መግለጫ በማውጣት ብቻ የሚፈታ እንዳልሆነ እሙን ነው። በመሆኑም ቅዱስ ሲኖዶስ ተጨማሪ ቀናትን ሳያባክን ከትግራይ አባቶች ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት በአካል በመገናኘት እና በመቀራረብ ውይይት እንደሚጀመር ይጠበቃል። ነገር ግን ይህ ሳይሆን ቀርቶ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ከተከናወነ ወደ ፊት ሊመጣ የሚችለው መከፋፈል እና ፈተና ከፊተኛው ይልቅ እጅግ የከፋ ሊሆን እንደሚችል መገመት አያዳግትም። ስለሆነም ይህ ጉዳይ ከወዲሁ በጥልቀት ታስቦበት እና ቅድሚያ ተሰጥቶት ከሹመት በፊት በትግራይ ካሉት ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በእርቁ ላይ እና ውሕደቱ ላይ ቢሠራ የበለጠ ፍሬያማ መሆን ይቻላል ብለን እናምናለን።ነገር ግ ን ይህ ጉዳይ ወቅታዊ እልባት ካልተገኘለት እርቁ እስኪፈጸም ድረስ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመቱ ለሌላ ጊዜ ማራዘመን እንደ አማራጭ ቢታይ መልካም ይሆናል ብለን የልጅነት ሃሳባችንን እናቀርባለን።

3. ወደ ፊት በሚኖረው የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ላይ የሚካተቱ ቆሞሳትን ከመምረጥ አኳያ በዘንድሮው ዓመት የተከሰተው ተመሳሳይ አይነት ችግር ወደ ፊት እንዳይፈጠር ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ የታወቀ ነው። ከዚህም አንጻር በወቅታዊው ችግር ውስጥ ተሳትፈው ለንሰሐ የዘገዩትን እና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ብሎም ምእመናንን በማሳዘን ለበደሉት በደል ይቅርታ እንኳን ለመጠየቅ ፈቃደኛ ሳይሆኑ፤ ነገር ግን በቅዱስ ሲኖዶሱ ሆደ ሰፊነት ግዝቱ የተነሳላቸው አባቶችን ከሹመት ማዘግየቱ ወሳኝ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ክብር የሚያስጠብቅ ነው። ይህም መንግሥት ወደ ፊት ሊያደርግ የሚችለውን አሉታዊ ተጽዕኖን ሊያስቀር ስለሚችል እነዚህን ቆሞሳት በአሁኑ ሹመት ላይ እንዳይካተቱ ሃሳባችንን እናቀርባለን።

4. ከላይ በተራ ቁጥር 1 ላይ እንደተገለጸው በዘንድሮው አመት ቤተ ክርስቲያንን የገጠማት ችግር ይህነው ሊባል የማይችል ነው። ከዚሁ ችግር ጋር በተያያዘ ሕይወት ጠፍቶአል፣ ለቁጥር የሚታክቱ ካህናት እና ምዕመናን ለእስር ተዳርገዋል፣ ከሥራ ገበታም ተፈናቅለዋል። በአጠቃላይ በካህናት እና በምዕመናን ዘንድ የመንፈስ አለመረጋጋት እንዳለ ይታወቃል።በእስር ያሉ እስካሁን ያልተፈቱ እንዳሉ ሆኖ ከሥራ ገበታቸው ላይ ተፈናቅለው ቤተሰቦቻቸው ችግር ላይ የወደቁም እናዳሉ የታወቀ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን የሕግ ቡድን በጉዳዩ ላይ እየሰራበት መሆኑን እናውቃለን። በሌላ አኳያ ከሕግ ውጭ ከተሾሙት መካከል ወደ ቤተክርስቲያን የልተመለሱ እና ችግሩን በውጭ ሆነው እያባባሱ ያሉ ግለሰቦች ከመኖራቸው ባሻገር፤ በጎጃም ውስጥ ራሳቸውን ጳጳስ አድርገው የሾሙም እንዳሉ ይታወቃል። ለእነዚህ ከሹመት ጋር ለታያዙ ችግሮች እልባት ሳይሰጥ ብሎም በእስር ላይ ያሉ እና ከሥራ ተፈናቅለው የሚገኙ ምዕመናን ከችግሩ መፈጠር አስቀድሞ ወደነበር ሕይወታቸው ሳይመለስ የሚደረግ የሹመት እንቅስቃሴ ለቤተ ክርስቲያኒቱ አንድነት አደጋ ላይ ይጥላል ብለን አናስባለን። እኒህ ሁሉ ያልተፈቱ ችግሮች ባሉበት በዚህ ወቅት አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳትን መሾም ችግሩን ማባባስ እና የተከፋፈለ ሲኖዶስን ለመፍጠር ከፍተኛ ዕድልን ይከፍታል። ብሎም ለአጽራረ ቤተ ክርስቲያን ተልዕኮአቸውን እንዲያስፈጽሙ መንገድ ከፍቶ መስጠት ነው። በአጠቃላይ ምንም እንኳን የኤጲስ ቆጶሳት መሾም የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በብዙ የሚያሳልጥ ቢሆንም፤ ከላይ በዚሁ አንቀጽ ላይ በዘረዘርናቸው የተለያዩ ምክንያቶች በዚህ ወቅት ኤጲስ ቆጶሳትን መሾም ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እጅግ የከፋ ሊሆን ይችላል ብለን እናምናለን።ስለሆነም እንደ የቤተ ክርስቲያን ልጅነታችን፤ እነዚህ ነገሮች ፍጹም እስኪስተካከሉ ድረስ ቅዱስ ሲኖዶስ ኤጲስ ቆጶሳትን መሾምን ላልተወሰነ ጊዜ ቢያራዝመው ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ሃገሪቱ ላይ ከተጋረጠባቸው አደጋ ሊድኑ ይችላሉ ብለን በማመን ሃሳባችንን ለቅዱስ ሲኖዶስ በታላቅ በትህትና እናቀርባለን።

5. በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በተለይም በአዲስ አበባ በመንግሥት ቤት እየፈርሰ ብዙ ምዕመናን ከቤት እየተፈናቀሉ ጎዳና ላይ እየተጣሉ ናቸው። “ከግፍ ብዛት የተነሣ ሰዎች ይጮኻሉ። ከኃያላንም ክንድ የተነሣ ለዕርዳታ ይጣራሉ።” (ኢዮ35፡9) እንዲል ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ወኪል ሆና በዚህ ዓለም የምታገለግል ስትሆን ይህንን በመንግሥት የሚደረግ የጭካኔ ተግባር እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች የሚታዩ የግድያ፣ የእስራት፣ የመፈናቀል እና የእንግልትን ግፍ እያየች እንዳላየች በጸጥታ ማለፏ ከእግዚአብሔር የተሰጣትን ኃላፊነት እንዳልተወጣች አመላካች ነው። በሁኔታዎቹ ሁሉ “ለተበደሉት አሁን እነሳለሁ” የሚለውም አምላክ እየታዘበ እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም። ስለሆነም ቀደምት ነቢያት ኋላም ቅዱሳን ሐዋርያት እውነትን በመናገር ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን ኃላፊነት በትጋት እና ሕይወታቸውን እስከሞት ድረስ በመስጠት ተጋድሏቸውን ፈጽመዋል። አሁንም ቤተ ክርስቲያን በችግር ቀን አለሁልሽ ለሚሉት፣ ከመቀነታቸው ፈትተው ቤተ ክርስቲያንን ለሚያሳንጹ፣ ቤተ ክርስቲያን ጥሪ ባደረገችላቸው ጊዜ ሁሉ ፈጥነው ምላሽ ለሚሰጡ ልጆቿ ከጎናቸው በመቆም በመንግሥት የሚደረጉ ግፎችን ልታወግዝ ይገባል። በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ኅብረት የዚህ ዓይነቱን የግፍ ድርጊት በጽኑ ያወግዛል፣ መንግሥትም በአስቸኳይ ለተበደሉት ከቤታቸው ለተፈናቀሉት እና ያለ አግባብ መከራ ለደርሰሰባቸው ኢትዮጵያውያን በሙሉ ለደረሰባቸው በደልና ካሳን በመክፈል ከቤታቸው ተፈናቅለው በሜዳ ለወደቁትም መጠለያ እንዲሰጣቸው እንጠይቃለን።


ወስብሐት ለእግዚአብሔር


ዋሺንግተን ዲሲ

መጋቢት 30 ቀን 2015 ዓ.ም

EOTCCPA-Position Statement-2023.pdf

 በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን ኅብረት የጋራ የአቋም መግለጫ 

 “በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!” 


“ኃጢአተኞች እነሆ ቀስታቸውን ገትረዋልና ፤ ፍላጻቸውንም በአውታር አዘጋጅተዋልና ፤ ልበ ቅኖችን በስውር 

ይነድፉ ዘንድ፤አንተ የሠራኸውን እነሆ እነርሱ አፍርሰዋልና ጻድቅ ግን ምን አደረገ ? “ መዝ 10 : ቁጥር 2-3 


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ በተከሰተው የጥር 14/ 2015 ዓ.ም ሕገ ወጥ ሹመት፣ የቀኖና እና የአስተዳደር ጥሰት ምክንያት ቤተ ክርስቲያን እስከ አሁን ድረስ በከባድ ፈተና ላይ ትገኛለች። 


“መግደል መሸነፍ ነው “ ይለን የነበረው መንግሥት በተግባር ተሸንፎ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች እና በተቆርቋሪ ወገኖች ላይ የፈጸመው እንግልት ፤ ስቃይ ፤ ድብደባ ፤ እስራት ፤ ግድያ፤ ማፈናቀል፤ ማሳደድ በእጅጉ የሚዘገንን ሆኖ ይገኛል። ከዚህ ጋር ተያይዞ አብያተ ክርስቲያናትን ማቃጠል፤ ቅርሶቿን መመዝበር፤ የአገልጋዮቿን ካህናት ክብር መዳፈር ፤ ሰብዓዊ መብት በአደባባይ መግፈፍ፤ አጠቃላይ የግፍ ጥግ የተፈጸመበት እና በግልጽ የታየበት ሲሆን፤ ገዥው መንግሥት ቤተ ክርስቲያንን ከርስቷ ከኢትዮጵያ ለመንቀል በትጋት እየሠራ መሆኑን ከተግባሩ ለመረዳት ተችሏል። ይህ ታሪክ ይቅር የማይለው ‘ሁሉን ለኔ ፤ ሁሉ የኔ” የሚል ስብስብ መሆኑን የራሱ ድርጊት አጋልጦታል ። 


ሀገርን ከነሙሉ ክብሯ ለትውልድ ለማሻገር ፈተናን ተቋቁሞ በጸሎት፤ ሠላማዊ ሠልፍ በማድረግ፤ ችግሩ ዓለማቀፋዊ ዕይታና ዕውቅና እንዲያገኝ በማድረግ ቤተ ክርስቲያን ያላትን ከፍተኛ የአመራር ብቃት ተጠቅማ የተቃጣባትን እኩይ ተግባር ለጊዜው የገታችው ቢመስልም፤ የማይተኛላትን ክፉ መንፈስ አጥብቆ መታገል የመላው ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ተከታይ ሁሉ ጥረት የሚጠይቅ ነው። ይህንንም ጥረት በተገቢው መንገድ ለመወጣት በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ ካህናትና ምእመናን አንድ ላይ በመሆን “በዋሽንግተን ዲሲ ና አካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን ኅብረት” አንድ ተቋም አቃቁመናል። የኅብረቱ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ ሀገራችን እና በተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ መንግሥት በፖሊሲ ደረጃ ቀርጾ፤ በሕዝቧ ላይ እስከዛሬ የፈጸመውን ፤ በቀጣይ የሚፈጸመውን ግፍና በደል እየተከታተለ በመረጃ የሚያጋልጥ ፤ በታሪክ መዝገብም እየከተበ፣ በትውልድ እንዲዘከር የሚያደርግ አካል ነው። በመሆኑም መንግሥት እጁን በሃይማኖት ጣልቃ አስገብቶ ጥንታዊትና፤ ሐዋርያዊት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን፣ ብሔር ብሔረሰብ በሚል ለመክፈልና ሀገራችንን ወደ ማትወጣው የእርስ በእርስ ግጭት ውስጥ ለመክተት ከሚያደርገው እንቅስቃሴ እጁን ሙሉ በሙሉ እንዲያነሳና የቤተ ክርስቲያኗን ብሎም የሀገሪቱን ደህንነት እንዲያስከብር ኅብረቱ በጽኑ እየጠየቀ የሚከተለውን ባለ 9 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቶአል፦ 


የአቋም መግለጫ 

1. ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ለማስከበር እስከ አሁን የሄደበት የአመራር ብቃት የሁሉንም ኦርቶዶክሳዊ ልጆቻችውን ልቡና የገዛ ፣ ሌሎች አካላትን ያስደመመ፤ አጽራረ- ቤተ ክርስቲያንን ያስደነገጠ ተግባር ነው። ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ መጋቢት 6 /2015 ዓ.ም. ባካሄደው ምልዓተ ጉባኤ ያወጣው ባለስድስት ነጥብ የአቋም መግለጫ ይህንኑ ያስቀጠለ ሆኖ አግኝተነዋል። በመሆኑም ይህን የቅዱስ ሲኖዶስን የአቋም መግለጫ ሙሉ በሙሉ የምንደግፍ ሲሆን ለተግባራዊነቱም ከቅዱስ ሲኖዶስ ጎን እንደምንቆም እናስገነዝባለን። 


2. በሕገ ወጥ መንገድ በተሾሙት ግለሰቦች ፣ እንዲሁም በደጋፊዎቻቸው እኩይ ተግባር ካህናት እና ምዕመናን፣ ላይ የደረሰው የሕይወት መጥፋት፣ የአካል እና የንብረት ጉዳት መጠንና ይዘት ዝርዝር በግልፅ ተመዝግቦ ለሰለባዎቹ እና ለቤተሰቦቻቸው ተገቢውን የሞራል፣ የገንዘብ፣ ብሎም የንብረት ካሣ እና ድጋፍ በመንግሥት በኩል እንዲደረግላቸው በአጽንዖት እያሳሰብን በቅዱስ ሲኖዶስ የተላለፈውን መመሪያ ተከትለው ጥቁር ልብስ በመልበሳቸው ከመንግሥት ሥራቸው የተፈናቀሉትም በአስቸኳይ ወደ ሥራቸው እንዲመለሱና የተቋረጠባቸው ደሞዝና ጥቅማ፣ጥቅም እንዲከፈላቸው እጠይቃለን። 


3. በሕገ ወጥ መንገድ ተሹመናል በሚሉት ግለሰቦችና እንዲሁም በደጋፊዎቻቸው እኩይ ተግባር የተጎዱ አድባራትና ገዳማት የንብረት ይዞታ፣ የቅርሳ ቅርስ፣ የከበሩ ንዋያተ ቅድሳት ወ.ዘ.ተ እንዲሁም በቁሳቁስ እና ገንዘብ ላይ የተፈፀሙ ምዝበራዎችና ዘረፋዎች በሰነዶች እና በእማኞች ምሥክርነት ተለይተው የጥፋቱና ጉዳቱ መጠን እንዲታወቅ ብሎም የጎደለው እንዲከፈል፣ የተበላሸው እንዲስተካከል እንዲሁም ወደ ቀድሞ ይዞታቸው እንዲመለሱ መንግሥት ኃላፊነቱን እንዲወጣ እንጠይቃለን። 


4. ለሕገ ወጦቹ ጥያቄ እና እርምጃ ተባባሪ አንሆንም በማለታቸው ምክንያት ከየአድባራቱና ገዳማቱ ከነበራቸው የሥራ ኃላፊነት የተገለሉ ካህናት እና መምህራነ- ወንጌል ወደ ቀደመ ሥራቸው እንዲመለሱና የተቋረጠባቸው ደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም በአስቸኳይ እንዲከፈላቸው እንጠይቃለን። 


5. ሕገ ወጥ ተሿሚዎቹ መነኮሳት የፈፀሙት ሃይማኖታዊ የቀኖና ጥሰት በዘርና በዘውግ ላይ አጠንጥኖ ሀገር በማፍረስና ሰላም በማሳጣት ቤተ ክርስቲያንን ለከፍተኛ አደጋ ያጋላጠ ተግባር ነው። በመሆኑም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለጵጵስና ምርጫ በፊርማ ማሰባሰብ ሽፋን የሌሎች ዕምነት ተከታዮችን በማስረግ እና በማሰባሰብ ጵጵስና በፖለቲካ ስሌት በሕዝብ ምርጫና በዘር ውክልና እንዲደረግ ውስጥ ለውስጥ እየተወጠነ ያለ ሴራ ነው። ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ከግንዛቤ በማስገባት ወደ ፊት በሚያከናውነው ሲመተ- ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ላይ ለዚህ ታላቅ ኃላፊነት የሚመረጡ ቆሞሳት ከምንም በላይ ያላቸውን መንፈሳዊ ሕይወት እና አስተዳደራዊ ክህሎትን ያማከለ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀኖና የተከተለ፣ፍጹም ከመንግሥት ተጽዕኖ ነጻ በሆነ መልኩና ቤተ ክርስቲያኒቱን በሚመጥን ሁኔታ እንዲያከናውን መንፈሳዊና የተቆርቋሪነት ኃሳባችንን ለቅዱስ ሲኖዶስ እንለግሳለን። 


6. የፌደራል እና የክልል የፍትሕ እና የጸጥታ አካላት ተገቢ ያልሆነ ወገንተኝነትን ፣አድሏዊነትን ፣ጣልቃ ገብነትን እና የሕግ ጥሰትን መፈጸማቸውን እንዲያቆሙ፤ እንዲሁም በብፁዓን አባቶችም ሆነ በአድባራት እና በገዳማት አስተዳዳሪዎች ላይ የማዋከብ እና የስም ማጥፋት ዘመቻቸውን እንዲያቆሙ እንመክራለን ፤ 

በተጨማሪም ለሕግ የበላይነት፣ ለእኩልነት፣ ለፍትህ እና ለሃይማኖት ነፃነት መረጋገጥ ተግተው እንዲሠሩ በአፅንዖት እንጠይቃለን። 


7. በሕገ ወጦቹና በሴራ ተባባሪዎቻቸው ረዳትነት ቤተ ክርስቲያንን እና የመንበረ ጵጵስና ቢሮዎች በመስበር በድፍረት የተያዙት ሀገረ ስብከቶች ወደቀደመ ይዞታቸው ሕጋውያን አባቶች በአስቸኳይ እንዲመለሱና አገልግሎት እንዲጀምሩ የሕግ አስከባሪዎች ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን ። በተጨማሪ መንግሥት ሕዝቡን በዘር በመከፋፈልና በመለያየት ከሚያደርገውን የዜጎች ጉስቁልና፣ መድሎ፣ እስራት እና ግድያ ተግባራት ሙሉ ለሙሉ እስኪቆሙ ድረስ፣ በሀገር ውስጥ እንዲሁም በውጭ የምንገኝ ኦርቶዶክሳዊያን እና መላው ኢትዮጵያውያን፣ አንድነታችንን ጠብቀን አሁንም ወደ ፊትም ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን እና ለሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድነት በጾም፣ በፀሎት እንድንቆም፣ ያለ መታከት ወደ እግዚአብሔር እንድናሳስብ ከዚህም ባሻገር አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ሁሉ በዓለም አደባባይ ድምፃችንን እንድናሰማ ጥሪ እናስተላልፋለን። 


8. የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ግልጽና ከማንኛውም የዘር አድሎና ሙስና የፀዳ እንዲሆን ዘመኑን የዋጀ የሰው ኃይል፣ የንብረትና የፋይናንስ አስተዳደር ማዕከላዊነቱን የጠበቀ፣ በባለ ሙያ የታገዘ ብሎም በተዋረድ ምዕመናንን በተገቢው ሁኔታ ያሳተፈ አሠራር እንዲኖር እና እንዲተገበር እንጠይቃለን ። 

9. በመጨረሻም ምንም እንኳን ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች በሀገራችን ካለው ህዝብ ብዛት ከፍተኛውን ቁጥር የያዝን ቢሆንም፣ ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ውስጥ የመጡ ገዥዎች መንፈሳዊነታችን እና ታጋሽነታችን ለሀገር ሰላም ከማሰብ አኳያ የተደረገ መሆኑን ባለመረዳታቸው እና እንደ ድክመት በመቁጠር ፣ ዝምታችንም ታክሎበት በቤተ ክርስትያን አስተዳደር ውስጥ ጣልቃ በመግባት ብሎም ጫናን በማሳደር ሕዝብን እና ቤተ ክርስቲያንን ሲበድሉ ኖረዋል፣ እየኖሩም ነው።በመሆኑም ሀገራችንን እና ቤተ ክርስቲያናችን አሁን ካሉበት የጥፋት አፋፍ ላይ እንዲደርሱ መሆናቸው እሙን ነው።ስለሆነም ሀገራችንን እና ቤተ ክርስቲያናችንን ከጥፋት ለመታደግ አልፎ ተርፎም ከፍ ባለ ማማ ላይ እንዲታዩ ለማድረግ መላው 

ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች፣ቸልተኝነትን በማስወገድ በፓለቲካ ውሳኔዎች፣ በኢኮኖሚ ዐቅም ግንባታ፣ በአስተዳዳርዊ ምርጫ እና መሰል እንቅስቃሴዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን አንድነት ለማስከበር፣ የሰብአዊ መብታቸንን ብሎም በሀገራችን ኢትዮጵያ አንድነትን፣ ፍቅርን፣ እውነተኛ ፍትህን፣ እኩልነትን እና ነፃነትን የሚያሰፍንና የተስተካከለ ሥርዓተ-መንግሥት እንዲተከል ለማድረግ በንቃት እንድንሰራ ጥሪአችንን እናቀርባለን ። 


ወስብሐት ለእግዚአብሔር 

ዋሺንግተን ዲሲ 

መጋቢት 11 ቀን 2015 ዓ.ም 

(March 20, 2023)



Moa Tewahedo Letter.pdf

Moa Tewahedo's Letter to International Communities 

Over the last 33 years Ethiopia had been ruled by a Stalinist Revolutionary group. It started with

a group called the Ethiopian People Revolutionary Democratic Front (EPRDF) that came to

power in 1991. This front is an offspring of the ethnio-Leninist group known as the Marxist-

Leninist League of Tigray (MLLT). With the end of the cold war and collapse of communism,

the Marxist Leninist element was made to fade away, under the guise of reform, but the basic

principles of the MLLT remained intact and fully implemented to rule the country.

In 2018 the EPRDF split into two factions of the Prosperity Party (PP) and the Tigrean Peoples

Liberation Front (TPLF). The power struggle between PP and TPLF led into a disastrous 2-

year war in North/Central Ethiopia resulting in the death and displacement of close to a million

people.

Following the signing of the peace deal between PP and TPLF the Prime Minster, Abiy Ahmed

Ali, has turned its gun on the followers and institutions of the Ethiopian Orthodox Tewahdo

Church (EOTC). This article attempts to narrate why a Prime Minster of a country wants to

wage a war on its own people, the political objective and practical solution to stop the carnage

that may result.

Colonel Abiy Ahmed Ali is the leader of PP, who was given the Nobel Peace Prize shortly after

he became the Prime Minster of Ethiopia. He is a master manipulator, who excel in creating an

emotional connection using various methods to advance his own agenda. In short, he is at the

center of all the crisis that are brewing in Ethiopia ever since he came to power. He presents

himself as a democrat, unifier and talks different thing to different people but his agendas are

to:

1. Remain in power as an unchallenged authoritarian and lifelong leader/king of Ethiopia;

2. Eliminate the Ethiopian Orthodox Church and replace it with the Prosperity theology,

sometimes referred to as the prosperity gospel, the health and wealth gospel, the gospel

of success, or seed faith.

3. Make his ethnic group, the Oromos, a dominant political and economic force through

illegitimate ethnic cleansing of non-oromos, particularly Orthodox Christians from the

Oromia region.

The EOTC is the largest religious group with more than 60 million followers and thousands of

historical churches and institutions throughout the country. The followers of EOTC comes from

all ethnic groups, are unified in their belief and thus developed communality and respect for

each other. This didn’t allow Abiy Ahmed Ali to achieve his goals and has become an obstacle

for his ambition. As a result he allowed extremist groups to target the Orthodox Christians for

ethnic cleaning and genocide. After the disastrous civil war in the north, his hands are now free

to start a new war against the followers of EOTC and its institutions.

The following is a very small sample of the destruction, persecution, and ethnic cleansing

carried out against the Orthodox Church and its followers, since Abiy Ahmed Ali came to power,

in the Oromia, Somali and Bensangul-Gumuz regions.

Somalia Region (South Eastern Ethiopia)

• August 6, 2018 in Jigiga, 7 churches were burnt and destroyed.

Examples:

https://borkena.com/2018/08/06/jijiga-29-people-killed-and-over-ten-churches-burned/

“Ethiopian Orthodox Church diocese head of Jijiga region, Like Kahnat Eyob Wondimu,

said that 7 Ethiopian Orthodox Tewahdo Churches were set on fire and 7 priests killed.

Among the burned churches is the recently inaugurated Holy Covenant Kidane Mihret

Menbere Tsebaot church”

https://www.acnmalta.org/ethiopia-10-churches-burned-30-killed-including-6-priestsin-

somali-region-acnmalta/#:~:

text=Ethiopian%20Orthodox%20Church%20diocese%20head,cost%20of%

207%20million%20birrs.

‘….in recent days, exploded in that part of Ethiopia, causing about 30 victims. The

Ethiopian Orthodox Church has paid a high price due to the spiral of violence:

according to information by local media, at least seven Orthodox churches have been

attacked and set on fire, and local sources speak of at least six priests and several

faithful killed.

http://www.fides.org/en/news/64614-

AFRICA_ETHIOPIA_Churches_burned_and_priests_killed_in_the_Somali_region

In July 2018, about 30 churches have been attacked, mainly in eastern and southern

Ethiopia, with more than half of them burned to the ground, according to the Amhara

Professionals Union (APU), a United States-based diaspora organization that has

attempted to track events.

In August 2018, an estimated 10 churches were burned in Ethiopia’s eastern Somali

region, resulting in 29 deaths, including of 8 priests. This March and April, another two

churches were attacked in the Somali region’s capital, Jijiga, resulting in 12 deaths.

In July, five churches were attacked with three torched in the southern Sidama zone —

killing three people.

“There have been at least 15 churches that were attacked, three of which were

completely burned down,” says Nathan Johnson, Africa regional manager for

International Christian Concern, a US-based nongovernmental organization that

monitors human rights of Christians and religious minorities around the world. “I have

only confirmed two cases in which priests have been killed in Ethiopia this year. It is

likely that this number is higher, though, as there are major tensions in the country.”

• July 2019, in Sidama region, which was part of the Southern Ethiopian administration

asked to create it’s own separate administration, that has nothing to do with the

Ethiopian Christians. The government was reluctant to grant regional autonomy and

following this protest many churches were burnt and many Christians were massacred.

https://borkena.com/2019/07/22/three-ethiopian-churches-burnt-in-sidama-death-toll-reaches-

60/

“Three Ethiopian churches in Sidama, Amaro and Burji diocese are burnt, reported DW

Amharic. The source said that it has confirmed the news from the church authorities.

Doya Michael, Gesaba-Gebrekristos and Chiro Amanuel are the churches that got

burned in the Sidama Dioceses of Ethiopian Orthodox Church (otherwise known as

Ethiopian Church) according to Megabi Haymanot Kesis Netsanet Aklog told DW

Amharic.

The attack was specifically launched against Ethiopian church. Some of the members of

the church who tried to protect the church are reportedly killed.

A disturbing image of a murdered priest in the area which was circulating on social

media has shocked many Ethiopians.

Several deacons had to run away to adjacent churches in Oromo region of Ethiopia

following the attack on the three churches, according to DW Amharic.”

“Churches belonging to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC) are being

burned to the ground throughout Ethiopia — one of the world’s most religious countries,

where about 98% of Ethiopians claim a religious affiliation. Church members have also

reportedly been killed while trying to protect their churches”.

“Since July 2018, about 30 churches have been attacked, mainly in eastern and southern

Ethiopia, with more than half of them burned to the ground, according to the Amhara

Professionals Union (APU), a United States-based diaspora organization that has

attempted to track events"

https://addisstandard.com/news-death-toll-rises-to-more-than-35-in-sidama-zonehundreds-

displaced-after-losing-properties/

“Quoting an eye witness, DW Amharic reported yesterday that the number of people

killed has risen to 34 and said 14 of the victims were killed in Hagere Selam town on

Friday July 19 when the police randomly opened fire at a group of civilians who were

marching toward a police station after a young man was killed the previous night”

• Even in Addis Ababa, the government police are practicing shooting to kill policy.

https://www.africanews.com/2020/02/06/ethiopia-police-orthodox-faithful-clash-overdisputed-

land-3-killed/

Police in the Ethiopian capital Addis Ababa clashed with Orthodox Christians over a

disputed piece of land leading to three deaths and several others injured, local portals

reported.

https://borkena.com/2022/01/21/ethiopia-oromia-police-killed-at-least-threeorthodox-

church-followers/

“In a latest string of attacks on the Ethiopian Orthodox Church, at least three people

were killed on Thursday ( January 21, 2022) when Oromia police opened fire on the

followers of the Ethiopian Orthodox Church who were in a religious procession as part

of Epiphany celebration in the capital Addis Ababa.”

https://newbusinessethiopia.com/crime/78-killed-in-ethiopia-following-oromo-activistfacebookpost/#:~:

text=The%20number%20of%20innocent%20people,far%2078%20people%2

0were%20killed.

The number of innocent people killed: Ethiopia following the Facebook post by an

Oromo ethic group Activist Jawar Mohammed has increased to 78, says a government

official.

https://www.ethiopiaobserver.com/2019/10/25/ethnic-amharas-targeted-in-killings-inoromia-

region/

October 25, 2019 | by Ethiopia Observer | 11

‘Four ethnic Amharas were killed and forty injured in Dodola district, west Arsi zone

on Wednesday and Thursday, following unrest caused by tensions between security

forces and influential journalist and activist Jawar Mohammed, local authorities and

residents said. Though the unrest was sparked because of anger at the federal

government for the alleged threat posed against Jawar, attacks have taken ethnic and

religious turn in some areas. Residents said that armed youth from the surrounding

areas of Dodola described as Quero stormed the town and torched homes and

properties owned by the Amhara ethnic groups, predominately Orthodox Christians. A

student by the name Zinabu was attacked and killed in his own house on Wednesday, a

resident of Dodola told VOA Amharic. Many Amharas later fled to Kidane Mehre

Church located in the outskirts of the town, seeking for shelter, according to the resident.

A grenade was thrown at the church several hours later, injuring dozens, the resident

said.’

The past month has seen an escalation in violent clashes across Ethiopia, with deep

polarization in Ethiopia leading to an ever-worsening human rights crisis. The ongoing

conflict in Tigray, as well as the December 23 massacre of more than 222 civilians in

the Benishangul-Gumuz Region (Reuters, December 25 2020), have seen ordinary

civilians bear the brunt of these clashes.

According to the United Nations High Commissioner for Refugees (UNHCR), more than

56,000 Ethiopian refugees have fled the country since early November.

https://addisstandard.com/news-alert-at-least-50-people-killed-as-protests-overassassinated-

oromo-artist-continue-police-confirm-arrest-of-jawar-mohammed-bekelegerba-

33-others/

At least 50 people killed as protests over assassinated Oromo artist continue; police

confirm arrest of Jawar Mohammed, Bekele Gerba & 33 others

https://www.theguardian.com/global-development/2020/aug/03/how-a-musiciansdeath-

unleashed-violence-and-death-in-ethiopia

160 people have died following the killing of Haacaaluu Hundeessaa, leaving the

ethnically and politically riven country more divided than ever.

https://time.com/5871217/ethiopia-protests-haacaaluu/

“The June 29 murder of Haacaaluu Hundeessaa, singer and activist, has triggered a

popular uprising in Ethiopia. TIME columnist Ian Bremmer described the protests in a

recent piece; since he wrote it the death toll has risen to at least 289, with over 7,000

detained. Internet services were shut down within hours of the assassination, and were

only restored after four weeks”.

https://www.nbcnews.com/news/world/dozens-killed-ethiopia-protests-over-singerhaacaaluu-

hundeessaa-s-death-n1232694

July 1, 2020, Source: Reuters

“ADDIS ABABA — At least 50 people were killed in Ethiopia's Oromiya region in

protests following the fatal shooting of a popular singer, a regional spokesman said on

Wednesday, laying bare splits in the prime minister's political heartland ahead of next

year's polls.”

https://www.reuters.com/article/us-ethiopia-protests-idUSKBN2430XO

ADDIS ABABA (Reuters) - Two people were killed on Thursday as Ethiopian security

forces scuffled with mourners trying to attend the stadium funeral of a singer whose

shooting this week sparked protests in which more than 80 people died, hospital officials

said.

Wellega Genocide

https://www.theguardian.com/world/2022/jul/05/villagers-massacred-westernethiopia-

says-state-appointed-body

“.message to AFP that the attack targeted members of the ethnic Amhara group in

Mender 20 (Village 20) in the Hawa Gelan district of Kellem Wollega. “One of our

investigators did talk to three eyewitnesses … hiding in a forest nearby,” the AAA said,

adding that the attack began at 6am local time (0400 BST) and was still going on when

he spoke to the witnesses around noon.

About 340 people were killed in the same region last month in one of the deadliest such

incidents for several years in Ethiopia.

https://www.aljazeera.com/news/2022/7/5/new-killings-in-ethiopias-oromia

“Citizens living in the Qellem Wollega zone of Oromia state have been massacred,” he

said, without giving details.

Conclusion

These are the tips of the attacks on Christians in Ethiopia and the Ethiopian Orthodox

Church. We have avoided some gruesome killing and mutilation of Christians not to

distress the readers of this information pack. However, we can supply day-by-day

accounts of the genocide that had been taking place in the last 5 years under Abiy Ahmed

Ali’s leadership.


Letter to Secretary of State.pdf

EOTCCPA Wrote a Letter to US Secretary Blinken

 March 10, 2023 

The Honorable Antony J. Blinken 

U.S. Secretary of State 

Office of the Secretary 

Room 7226 

Harry S. Truman Building 

2201 C Street, NW 

Washington, D.C. 20520 

In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, One God Amen. 

Dear Secretary, Blinken: 

Our warmest greetings to you and your resolute staff in the State Department. On behalf of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC) clergies in the DC metro area, youth of the church, and the faithful, we would like to bring an urgent matter to your attention. 

The EOTC is one of the ancient churches with apostolic succession, it maintained the dogmatic and canonical teachings of the patristic fathers. The church has been a pivotal instrument to maintaining peace, unity and integrity of the country and around the Horn of Africa. Expanding its presence, it opened its first church in the US in New York city, during President Kennedy’s Presidency and continued opening more churches in various States over the last sixty years. Just to highlight, at present time there are more than 320 churches across the US that provides services in English and Amharic for close to a million citizens. This spread of the church across the US helped for the creation of good citizens and reducing criminals. Our Christian brothers and sisters are currently serving in the US military, in Federal agencies, in state legislative branches, in private business and public companies. Indeed, our churches plays a discernible role in helping our patrons demonstrate and discharge their respective responsibilities ethically and morally with a high standard and dignity. They participate in political campaigns to assist potential candidates at different offices both in Federal and state governments. 

The urgent matter we are bringing to your attention affects solely over sixty million Orthodox Christians residing in Ethiopia in person and over three million living outside. The issue is extremely urgent and time-sensitive, affecting the peace and stability of the country, with a potential for massive unrest and violence in Ethiopia and neighboring countries. As it is clearly reflected in the most recent debacle related to the Ethiopian Orthodox church, the authorities in power have been aiming to divide the Orthodox church with the pretext to create a separate synod for the Oromo nations and dismantle the country. Had it not been due to the Orthodox church to glue the nation together, the country would have been split among 84 pieces long ago, prompted by to the most flawed constitution that has been designed to dismember the country. The church has always served as a bridge across all ethnic groups, cultures, languages, localities, and regions in the country, promoting peace, stability, and security in the society as well as tolerance and respect among all citizens. It played significant roles maintaining the unity of the country. For the dividing and rule government it is imperative to attack the church so that it can effectively disintegrate the country and promote just Single ethnic group ruling state and subdue the remaining 83, promote corruption and enslave other ethnic groups. 

In order to disintegrate the church the government secretly recruited three bishops, who are Oromos that is similar to the authorities ethnic group, from within the church’s synod. After recruiting these bishops, the government orchestrated unlawful ordination of twenty-six bishops without the knowledge and approval of the Holy synod, violating the doctrine and canon of the church. The newly formed group secretly conspired to go against Orthodox Christian Church unity by contriving divisive schemes with the intent of promoting ungodly and ethnically motivated objectives antagonistically to the Apostolic succession and core values of the EOTC. The EOTC has a strong and established apostolic church and maintained its integrity for over two millenniums, since the first century as descended from the disciples of Jesus Christ. 

In the news conference the prime Minister held at the end of January he asserted recognition of the unlawfully ordained people as church bishops for the Oromo ethnic group, contrary to the Church Holy Synod Canonical position. In the same briefing session, he aggressively instructed his Cabinets not to get involved in any manner to bridge the split caused in the church. His autocratic behavior and dictatorial act further sparked massive, and historical demonstration in the capital city, Addis Ababa, and various cities across the country as well as in Europe, Australia Canada and here in the various states of USA including the ones at the State department and across the White House opposing his unwarranted incursion in the church’s internal affair. The international outcry and opposition both in the country and outside forced the prime minister to reconsider his act and tried to act instead as an arbitrator seeming to act like he is independent and had no awareness of the matter beforehand. The purpose of his arbitration role was to temporarily calm the public, not truly to eradicate the difference or mitigate the consequences of it. 

Following the arbitration: 

The Amhara, Gurage and other ethnic groups were displaced from the Oromia region because of their ethnicity and Orthodox Christian faith. Since the Prime minister came to office, Ethiopians had the hoped to see more democratic and uniting governance, however the reality is the opposite, the hope is completely vanished. Instead of uniting the country, due to poor leadership and arrogance on the part of the leaders, for the past three years, the country engaged in a senseless civil war in the norther part. As a result, we lost a million productive lives, basic infrastructures were destroyed, and significant displacements took place. These acts of violence, persecution and violation of basic human rights and religious freedom become a norm. It has become a day- to- day routine to breaking churches, oppressing Christians, jailing, and killing Christians. It becomes impossible for Christians to worship and freely exercise their religious and constitutional rights. 

also became clear that the intention of the government is to destroy the Christian faith in a systematic method. The Orthodox Christians are terrified and worried about their safety and lives. These noxious trends potentially will lead to a series of turmoil and blood shed that will eventually culminate into religious civil war. 

Mr. Secretary, the world has witnessed a tragedy in Rwanda in 1994 due to ethnic cleansing. The unwarranted clash between the Tutsi and Hutu tribes led to the loss of millions of Rwandese for no reason. The conflict between just two ethnic groups has costed millions of lives in Rwanda and left historical scar in the history of humankind. In a country like Ethiopia which is comprise of eighty-four ethnic groups, you can imagine the destruction and loss of life that would ensue due to the failed governance of Abiy Ahmed. The problem will not halt there rather will spill over to other countries igniting instability in the Horn of Africa, it also will open a gate for potential Terrorists in the continent. 

We, therefore, humbly appeal to your prudent leadership to influence The Abiy regime to stop unconstitutional acts against the Christian citizens and the various ethnic groups. The current problem in Ethiopia is a major issue that falls under the jurisdiction of your office within the department of the Ministerial to Advance Religious Freedom. As the US is known for advocating for religious freedom and human rights. We strongly believe that your office has the capability to exert diplomatic pressure to the Abiy regime to stop, every undemocratic and inhumane acts implemented by his ruling to destroy certain ethnic groups and the Orthodox church from the land. As you are heading to Ethiopia in your upcoming trip to Africa, we put great trust in your ability to discuss the challenges facing Ethiopia, including persecutions and discriminations, to promote greater respect and religious liberty for all. In the spirit of that mission, you are promoting to support freedom and democracy in Africa and across the world, we are respectfully submitting this letter to Your Honor with the hope you will promptly take actions, to reverse the course. 

Dear Mr. Secretary, if you need further information on the matter, we are available at your convenience to discuss with your office and take part finding appropriate means to resolve the crisis before things go out of hand and inflict colossal damages in the country perhaps in the Horn of Africa. 

Thank you so much for your attention and kindness! 

Sincerely,